Tuesday, May 30, 2023
- ማስታወቂያ -
- ማስታወቂያ -

ከተሽከርካሪ የሚመነጭ በካይ ጋዝን ለመቀነስ የሚረዳ አዲስ ቴክኖሎጂ ቀረበ

- ማስታወቂያ -

ተዛማጅ ፅሁፎች

ከተሽከርካሪዎች የሚወጣውን የበካይ ጋዝ ልቀት በ80 በመቶ መቀነስ ይችላል የተባለና ጣልያን ሠራሽ ‹‹ሱፐርቴክ›› የተባለ ቴክኖሎጂ ሥራ ላይ ሊውል ነው፡፡ ቴክኖሎጂው የበካይ ጋዝ ልቀትን በመቀነስ፣ ብክለትን ከመቆጣጠር ባሻገር እስከ 12 በመቶ የነዳጅ ፍጆታን እንደሚቀንስ ተነግሮታል፡፡ ለአውቶሞቢሎች፣ ለሚሳብ ተሽከርካሪዎች፣ ለጭነት፣ ለአውቶብሶችና ለረዣዥም ተሽከርካሪዎች እንዲሁም በነዳጅ ለሚሠሩ ጀነሬተሮች የሚያገለግል ሲሆን፣ የገበያ ዋጋውም ከ25 እስከ 100 ዩሮ እንደሆነ ታውቋል፡፡ በ30 አገሮች ውስጥ የሚሰጠው አገልግሎት ሱፐርቴክ ቴክኖሎጂን የሚያስመጣው ኢዙኬም ትሬዲንግ የተባለ አገር በቀል ኩባንያ ነው፡፡

በመኪና የነዳጅ መያዣ ቋት (ሳልቫቲዮ) ውስጥ የሚገጠመው ይህ ቴክኖሎጂ፣ ጭስ ማውጫን የማፅዳት ባህሪይ እንዳለው፣ የካርቦን ዝቃጭን እንደሚቀነስ፣ ለሞተር የበለጠ ዕድሜን በመስጠት በየጊዜው የሚደረግን ጥገና እንደሚቀንስ ስለቴክኖሎጂው ገለጻ የሰጡት አቶ ዮሐንስ ወልደገብርኤል አስረድተዋል፡፡

የኩባንው ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ አብዱላዚዝ ከማል፣ ቴክኖሎጂው በተለያዩ የዓለም ክፍሎችና በአብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገሮች ጥቅም ላይ መዋሉን ተናግረዋል፡፡ ቴክኖሎጂውን ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት ጣልያን አገር ከሚገኘው የምርቱ ባለቤት ኩባንያ ጋር በተናጠል መፈራረማቸውን፣ የገበያ ሽፋኑንም በምሥራቅ አፍሪካ በሚገኙ አገሮች ሁሉ ተደራሽ የማድረግ ዕቅድ መነደፉን ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ በነዳጅ ለሚሠሩ ጀነሬተሮች ቴክኖሎጂው በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ሥራ ላይ እንደሚውል ገልጸው፣ ‹‹ቴክኖሎጂውን ወደ አገር ውስጥ ለማስገባት ከባንኮች የውጭ ምንዛሪ ጠይቀናል፡፡ ገንዘቡ እጃችን ሲገባ ወደ አገር ውስጥ የማስገባቱን ሥራ እንጀምራለን፡፡ ከቀረጥ ነፃ እንድናስገባ ለመንግሥት ጥያቄ አቅርበናል፤›› ብለዋል፡፡ አቶ አብዱላዚዝ ይህንን የተናገሩት፣ እሑድ ኅዳር 25 ቀን 2009 ዓ.ም. በመንገድና ትራንስፖርት ባለሥልጣን ጽሕፈት ቤት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት ነበር፡፡

ከጊዜ ወደ ጊዜ እንዲህ ያሉ ቴክኖሎጂዎች ብቅ እያሉ ሲሆን ከዚህ ቀደም የጃፓን ሥሪት ቴክኖሎጂ  በአሁኑ ወቅት በዓለም ትልቅ መነጋገሪያ የሆነውን የበካይ ጋዞች ልቀትን ለመቆጣጠር ብዙ ጥረቶች እየተደረጉ ይገኛሉ፡፡ ከፍተኛ የሆነው የበካይ ጋዝ ልቀት በኢንዱስትሪ ከበለፀጉት አገሮች የሚለቀቅ ሲሆን፣ እንደ ኢትዮጵያ ባሉት ታዳጊ አገሮች የሚለቀቀው የበካይ ጋዝ መጠን ከሌሎቹ አንፃር ሲታይ እጅግ አነስተኛ ነው፡፡ የበካይ ጋዝ ምንጭ ከሆኑት መካከል ትራንስፖርት አንዱ ነው፡፡ በአገሪቱ 30 በመቶ የሚሆነው የበካይ ጋዝ ልቀት ከተሽከርካሪዎች የሚወጣ እንደሆነ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ እ.ኤ.አ. በ2012 የወጣ ሪፖርት እንደሚያሳየው አዲስ አበባ ከተማ 4.8 ሚሊዮን ቶን ካርቦንዳይኦክሳድ ጋዝ ወደ ከባቢ አየር ትለቃለች፡፡ ከዚህ ውስጥ 47 ከመቶ ከተሽከርካሪዎች የሚለቀቅ ነው፡፡ ካለው የሕዝብ ብዛት አኳያ በአገሪቱ ያለው የተሽከርካሪ ቁጥር በእጅጉ አናሳ ነው፡፡

ከ90 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ በሚኖርበት አገር ውስጥ የተሽርካሪዎች ብዛት 708,000 ብቻ ነው፡፡ ይህንን ያህል ተሽከርካሪ ባለበት ሁኔታ ከተሽከርካሪዎች የሚለቀቀው የበካይ ጋዝ መጠን ከሚጠበቀው በላይ መሆኑ በአብዛኛው በዕድሜ የገፉና ያረጁ ተሽከርካሪዎች በብዛት መኖራቸው አንዱ መንስዔ ሲሆን፣ የሚነጨው በካይ ጋዝ መጠንም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመምጣቱ አሳሳቢ ሆኗል፡፡

ይህም ሆኖ በአገሪቱ የአረንጓዴ ልማት ስትራቴጂ የጥናት ሰነድ መሠረት ከፍተኛውን የበካይ ጋዝ የሚያመነጩት የግብርናና የደን ምንጣሮ ተግባራት ናቸው፡፡

 

 

spot_img
- Advertisement -spot_img

የ ጋዜጠኛው ሌሎች ፅሁፎች

- ማስታወቂያ -

በብዛት ከተነበቡ ፅሁፎች