- Advertisement -

ከጅምሩ ያልተመጣጠነ የሚመስለው የፕሪሚየር ሊጉ ፉክክር

የዓመቱ የፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ከመጀመሩ ቀደም ብሎ በክረምቱ ወራት ክለቦች ሲዘጋጁ ቆይተዋል፡፡ በርካታ ተጨዋቾች በሚሊዮን ብሮች ተዘዋውረዋል፡፡ ከክለብ ክለብ የተደረጉ ሽያጮች፣ የአዳዲስ አሠልጣኞች ሹመት፣ የነባሮች ስንብትና ሌሎችም ሲካሄዱ የቆዩ የፕሪሚየር ሊጉ ክንውኖች ናቸው፡፡

ሁሉም ክለቦች በየፊናቸው ሲያደርጉት የነበረውን ዝግጅት አጠናቀው መደበኛውን ውድድር ማከናወን ጀምረዋል፡፡ ይሁንና የበርካቶቹ ክለቦች የሜዳ ውስጥ እንቅስቃሴ ግን ዝግጅታቸው ምን ይመስል እንደነበር የሚጠቁም ነው፡፡ አብዛኞቹ ከጅምሩ ተዳክመው የታዩበት በጣት የሚቆጠሩ ክለቦች ደግሞ ከወዲሁ አስፈሪ የሆኑበት እንቅስቃሴ እየታዩም ይገኛል፡፡

በተጨዋቾች አመላመል፣ በተጨዋቾች የሜዳ ውስጥ እንቅስቃሴ፣ ብቃትና የመሳሰሉትን ጨምሮ የአሠልጣኞች አንብቦ የማስተካከል፣ በተቃራኒ ቡድን ላይ ብልጫ የመያዝና ሌሎችንም ነጥቦች መነሻ በማድረግ የሊጉ የተፎካካሪነት አቅም ሲታይ፣ ክለቦች የሚያሳዩት የብቃት ልዩነት የዓመቱ መርሐ ግብር ከግማሽ መንገድ ሳይደርስ እንዳይጠናቀቅ ሥጋት የጫረባቸው በርካቶች ሆነዋል፡፡

የአገሪቱ እግር ኳስ በተለያዩ የውድድር ይዘት (ፎርማት) እስከ 1990 ዓ.ም. ድረስ በተለያየ መልኩ ሲካሄድ ቆይቷል፡፡ ከ28 ዓመት በኋላ ግን አሁን ድረስ ሲጠራበት የቆየውን ‹‹ፕሪሚየር ሊግ›› የውድድር ይዘት ይዞ ቆይቷል፡፡ አገሪቱ የምትከተለውን የፌዴራሊዝም ሥርዓት ተከትሎ በተዟዙሮ ሲከናወን የቆየውን ይህንኑ የውድድር ይዘት ለእግር ኳስ ዕድገት የማይበጅ መሆኑን በመጥቀስ አንዳንዶች ይከራከራሉ፡፡ በሌላ ወገን ደግሞ ለእግር ኳሱ ውድቀት ችግሩ የውድድሩ ይዘት ሳይሆን እግር ኳስ በተለይ በአሁኑ ወቅት ከደረሰበት የዕድገት ደረጃ አኳያ ሊሰጠው የሚገባው ትኩረት ማነስ መሆኑን የሚገልጹ አሉ፡፡ ለአብነትም ለአገሪቱ እግር ኳስ መነሻነት የሚጠቀሱት እንደ አዲስ አበባ የመሳሰሉ ከተሞች ከትምህርት ቤት ጀምሮ በየደረጃው የሚከናወኑ መሠረተ ልማቶች ስፖርቱን ያማከሉ አለመሆናቸው በዋናነት ተጠቃሽ እንደሆነ በማሳያነት የሚያቀርቡም አሉ፡፡

ከ1980ዎቹ ጀምሮ የእግር ኳስ ጨዋታ በሚከናወንባቸው ቦታዎች ሁሉ እንደማይጠፋ ይናገራሉ፡፡ አቶ ርስቱ ተሰማ በክለብ ደረጃ በቀድሞ መጠሪያው የመብራት ኃይል ደጋፊ እንደነበሩም ያስረዳሉ፡፡ መብራት ኃይል የአሁኑ ኢትዮ ኤሌክትሪክ በእግር ኳሱ የነበረውን አቋም እንኳ ማቆየት ባለመቻሉ ምክንያት ደጋፊነታቸውን ትተው ተመልካች በመሆን መዝለቃቸውን ይናገራሉ፡፡ እንደ አቶ ርስቱ አሁን አሁን የቀድሞ ክለባቸው ደጋፊዎችን ጨምሮ ሰዎች ስለፕሪሚየር ሊጉ ሲከራከሩ በሚሰሙበት ሰዓት እንደሚገረሙም ያስረዳሉ፡፡ አስተያየት ሰጪው ለዚህ የሚሰጡት ምክንያት የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ከተመሠረተበት ከ1990 ዓ.ም. ጀምሮ ቅዱስ ጊዮርጊስ 14 ጊዜ የዋንጫ ባለቤት ሆኖ የዘለቀበትን የውድድር ሒደት ይጠቅሳሉ፡፡

ሁለት አሠርታትን ባስቆጠረው የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በ1990 ዓ.ም. የመጀመሪያውን ዋንጫ ያነሳው የቀድሞው መብራት ኃይል የአሁኑ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ሲሆን፣ ቅዱስ ጊዮርጊስ ወደ ፕሪሚየር ሊጉ ባደገበት በ1991 ዓ.ም. እና በ1992 ዓ.ም. አከታትሎ ወስዷል፡፡ በ1993 ዓ.ም. ኢትዮ ኤሌክትሪክ ለሁለተኛ ጊዜ ዋንጫውን ሲያነሳ፣ በ1994 እና 1995 ዓ.ም. ደግሞ ቅዱስ ጊዮርጊስ አከታትሎ በመውሰድ የዋንጫ ባለቤት ሆኗል፡፡

- Advertisement -

በ1996 ዓ.ም. ሐዋሳ ከተማ ሲወሰድ፣ 1997 እና 1998 ዓ.ም. አሁንም ቅዱስ ጊዮርጊስ ወስዷል፡፡ በ1999 ዓ.ም. በክለቦችና በፌዴሬሽኑ መካከል በተፈጠረው አለመግባባት የአዲስ አበባ ክለቦች ባልተሳተፉበት ሐዋሳ ከተማ ለሁለተኛ ጊዜ የዋንጫው ባለቤት የሆነበትን ታሪክ አስመዝግቧል፡፡ ሲቀጥል ቅዱስ ጊዮርጊስ በ2000፣ በ2001 እና በ2002 ዓ.ም. ሦስት ጊዜ አከታትሎ በመውሰድ ዋንጫውን የግሉ አድርጓል፡፡ በ2003 ዓ.ም. ኢትዮጵያ ቡና ሲወስድ፣ በ2004 ዓ.ም. እንደገና ቅዱስ ጊዮርጊስ ወሰዷል፡፡ በ2005 ዓ.ም. ደግሞ ደደቢት የዋንጫ ባለቤት ለመሆን በቅቷል፡፡ ከዚያ በኋላ ማለትም በ2006፣ በ2007፣ በ2008 እና በ2009 ዓ.ም. ለአራት ተከታታይ ዓመታት ቅዱስ ጊዮርጊስ ያለ ተቀናቃኝ ሻምፒዮን መሆኑን አስጠብቆ ቆይቷል፡፡

የዘንድሮው መርሐ ግብር አጀማመርን አስመልክቶ አስተያየት ሰጪው፣ የቅዱስ ጊዮርጊስና ሌሎች ቡድኖች በሜዳ ላይ በሚያሳዩት ወቅታዊ እንቅስቃሴ ልዩነት ከወዲሁ እየታዩ መሆኑን ያስረዳሉ፡፡

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

ለስፖርቱና ለተቋማቱ ዕፎይታ የሰጠው አገር በቀሉ ጅምር

ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ ሲያስወጡ የነበሩ የስፖርት ትጥቆች በአገር ውስጥ እንዲመረት መደረጉ፣ ለስፖርቱ ተቋማትና ለዘርፉ የሚኖረው ፋይዳ ቀላል አለመሆኑ ይወሳል፡፡ ከዚህ አንፃር በሐዋሳ ከተማ የሚገኘው...

የኢትዮጵያ ስፖርት አካዴሚ ጉዞን የቃኘው የአርባ ምንጩ መድረክ

በቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ትዕዛዝ እንዲገነባ የሆነው፣ ቀደም ሲል የኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዴሚ በአሁኑ የኢትዮጵያ ስፖርት አካዴሚ ከምስረታው ጀምሮ ከሁሉም የአገሪቱ ክፍሎች በስፖርቱ...

ሃዋሳ ከአዲስ አበባ ቀጥሎ የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ መዳረሻ መሆኗ ተነገረ

በመስፍን ሰለሞን በሃዋሳ ከተማ የተካሄደው ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ በነዋሪው ዘንድ እያሳደረ የመጣውን ተወዳጅነትና ቅቡልነት እንደተላበሰ በስኬት ተካሂዷል፡፡ ባለፈው እሑድ የካቲት 2 ቀን 2017 ዓ.ም. ለ13ኛ ጊዜ...

‹‹የፕሮዤ ተሰማ›› ፍሬ የሆነው የአፍሪካ ኦሊምፒክ ተቋም አኖካ እና ኢትዮጵያ ያልታጨችበት ምርጫ

በአሁኑ ወቅት ሃምሳ አራት የአፍሪካ ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎችን ባንድነት ያቀፈው የአፍሪካ ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማኅበር (አኖካ)፣ ለመጪው አራት ዓመታት የሚመሩትን ፕሬዚዳንትና ሥራ አስፈጻሚዎችን በመጋቢት...

ስያሜውን ብቻ ሳይሆን መሥፈርቱን ሳያሟላ የቆየው የጃንሜዳ ኢንተርናሽናል አገር አቋራጭ ሻምፒዮና

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ‹‹ጃንሜዳ ኢንተርናሽናል አገር አቋራጭ ሻምፒዮና›› በሚል ከአራት አሠርታት በፊት በአዲስ አበባ ከተማ ያስጀመረው ሩጫ ዘንድሮ 42ኛውን ሻምፒዮና ባለፈው እሑድ ጥር 25...

ከዓመታት በኋላ የተጀመረው የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ውድድር

ለስድስት ዓመታት ተቋርጦ የቆየው የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ውድድር በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ሶዶ ከተማ ጥር 27 ቀን 2017 ዓ.ም. መካሄድ ጀምሯል፡፡ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር...

አዳዲስ ጽሁፎች

የጤናው ዘርፍ ባለፉት ስድሥት ወራት

የወባ በሽታ ከሰሃራ በታች በሚገኙ የአፍሪካ አገሮች ዋነኛ የጤናና የማኅበራዊ ቀውስ መንስዔ ነው፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት እ.ኤ.አ. በ2024 ያወጣው መረጃም 263 ሚሊዮን ሰዎች የወባ...

የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት በባለሙያ ዓይን

(በጎ ጎኖችና እርምት የሚፈልጉ ጉዳዮች) በዮሐንስ መኮንን በጥር ወር 2016 ዓ.ም. የአዲስ አበባ ዋና ዋና ኮሪደሮችን በማዘመን ከተማዋን ለነዋሪዎቿና ለጎብኚዎቿ ምቹ ያደርጋታል የተባለ ፕሮጀክት በ43 ቢሊዮን...

በልዩነት ውስጥ ሆነንም እስኪ እንነጋገር

በገነት ዓለሙ ዴሞክራሲ መብቶችና ነፃነቶች የሚሠሩበት የሕዝብ አስተዳደር ነው፡፡ ሰብዓዊ መብቶችንና ነፃነቶችን መኗኗሪ ያደረገ ሥርዓት ነው፡፡ እነዚህ መሠረታዊ መብቶችና ነፃነቶች በተፈጥሮ የተገኙ፣ ሰው በመሆናችን ብቻ...

ለጤናማ የትራፊክ ፍሰትና ለመንገድ ደኅንነት ቅጣት መጣል ብቻውን መፍትሔ አይሆንም!

በአዲስ አበባ ከተማ ለተሽከርካሪዎች ምቹ የሆኑ መንገዶችን እየተመለከትን ነው፡፡ ከአዳዲሶቹ መንገዶች ባሻገር አንዳንድ ነባር መንገዶች የማስፋፊያ ሥራ ታክሎባቸው አገልግሎት ላይ ውለዋል፡፡ ከኮሪደር ልማቱ ጋር...

የግጭት አዙሪት ውስጥ ሆኖ የአፍሪካ ማዕከል መሆን ያዳግታል!

የአፍሪካ ኅብረት 38ኛው የመሪዎች ጉባዔ በአዲስ አበባ ሲካሄድ ብዙ ትዝ የሚሉ ጉዳዮች አሉ፡፡ እጅግ በጣም አሰልቺ፣ ውጣ ውረድ የበዛበትና ታላቅ ተጋድሎ ተደርጎበት ከከፍተኛ ዲፕሎማሲያዊ...

አገሬ ምንተባልሽ – ልብ ያለው ልብ ይበል

በቶማስ በቀለ ይቺ አገራችን ብዙ ተብሎላታልም፣ ብዙ ተወርቶባታልም፣ አገሪቱ በቅኝ ያልተገዛች ብቸኛ አገር (ላይቤሪያን ጨምሮ) ከመሆኗ አኳያ የሚነገርላት ብዙ ጥሩና የሚገርሙ ነገሮች ያሉትን ያህል፣ ከረሃብ...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን