Wednesday, October 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናየአሜሪካ ኤምባሲ በኢትዮጵያ የሚታየው ግጭት አሳስቦኛል አለ

የአሜሪካ ኤምባሲ በኢትዮጵያ የሚታየው ግጭት አሳስቦኛል አለ

ቀን:

የአሜሪካ ኤምባሲ በጨለንቆና በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በተነሱ ግጭቶች የሰዎች ሕይወት በመጥፋቱና የአካል ጉዳት በመድረሱ እጅግ እንዳሳሰበውና እንዳዘነ ገለጸ፡፡ ኤምባሲው በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ ለተጎጂ ቤተሰቦችና ወዳጆች መጽናናትን ተመኝቷል፡፡

ከሁለት ዓመታት በፊት ጀምሮ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች በተከሰቱ ግጭቶች የሰዎች ሕይወት መጥፋቱና ንብረት መውደሙ ይታወሳል፡፡ በቅርቡም በተለያዩ ምክንያቶች በአማራ፣ በትግራይና በኦሮሚያ ክልሎች ያሉ ዩኒቨርሲቲዎች የመማር ማስተማር ሥራ እንደ ተስተጓጎለ ይታወቃል፡፡

የአሜሪካ ኤምባሲም በጨለንቆና በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች በተከሰቱ ግጭቶች የተሳተፉትን መንግሥት ተጠያቂ እንዲያደርግና የዜጎቹን ደኅንነት እንዲያስጠብቅ ጥሪ አቅርቧል፡፡

የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚደነቀውንና አብሮት የቆየውን ብዝኃነት የማክበር ልምድ እንዲጠብቅና ልዩነቱን በጋራ መፍታት ይችል ዘንድ ዘዴዎችን እንዲቀይስ በማሳሰብ ኤምባሲው መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

[ክቡር ሚኒስትሩ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው በቴሌቪዥን የሚተላለፈውን ዜና በመገረም እየተመለከቱ አገኟቸው]

ምንድነው እንዲህ ቀልብሽን የሳበው? ስለሰላም ኖቤል ሽልማት ዜና እየተመለከትኩ ነበር። እና...

የወሎ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ መመሥረትና የአማራ ክልል ጥያቄ

አማራ የኢሕአዴግ አንዱ መሥራችና አጋር ከሆነው ብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ...

የሽንኩርት ዋጋ ሰማይ የነካበት ምክንያት ምንድነው?

ባለፉት ሁለትና ሦስት ሳምንታት የሸማቾችን ኪስ ካስደነገጡ መሠረታዊ ከሚባሉ...

የአዲስ አበባ ንግድ ምክር ቤት ኤግዚቢሽን ማዕከልን እንዲያስተዳድር የተሰጠው ኮንትራት ለምን ተቋረጠ?

በአዲስ አበባ ከተማ ለንግድ ትርዒት ዝግጅት ብቸኛ በመሆን የሚጠቀሰው...