‹‹ሰዎች ለተሻለ ሕይወት ከአንድ አገር ወደ ሌላው ሲሰደዱ፣ ስለራሳችን ጥቅም ብቻ ሳይሆን በማሕጸን ውስጥ ስላለ ሕፃንም ይሁን ስለ እናቱ አልያም ስለ ቤተሰቡም ማሰብ አለብን፡፡ ይህንን ኃላፊነታችንን ለመወጣት ስለምንሻ ከተመራጩ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ውይይት እናደርጋለን፡፡››
ተሰናባቹ ሊቀ ጳጳስ ጆሴፍ ኩርት፣ ሰሞኑን በአሜሪካ የካቶሊክ ጳጳሳት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ጳጳሳቱ አዲሱ የትራምፕ አስተዳደር ለተሻለ ሕይወት ወደ አሜሪካ ለሚጎርፉት መፃተኞች ‹‹ተጨባጭ ዕርምጃ›› እንዲወስድ ሊቀጳጳስ ጆሴፍ በአሜሪካ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ የቅስቀሳ ሒደት ሰብአዊ መብትን የሚጋፉ አካሔዶች እንደነበሩ አስታውሰው፣ ‹‹ላለፉት 99 ዓመታት እንዳደረግነው፣ ከዚህ አልፈን በሥልጣን ያሉትን አመራሮች በማክበር እውነቶችን የተመረኮዘ መንገድ መከተል አለብን፡፡ ለውጥን በመፈለግም በሁለቱም ኮንግረሶች ከዶናልድ ትራምፕ አመራሮች ጋር እንወያያለን፤›› በማለት አስረግጠው ተናግረዋል፡፡