Sunday, March 26, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
እኔ የምለዉብሶት የበዛበት ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን

ብሶት የበዛበት ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን

ቀን:

ጥበበ ሙኤል ረንጅ

ባለፉት በርካታ ዓመታት በኢትዮጵያ ውስጥ ከፍተኛ የአሠራርና የአስተዳደር ለውጥ ከተደረገባቸው ነገሮች ውስጥ የግብር አከፋፈልና አሰባሰብ ለመሆኑ አከራካሪ አይመስለኝም፡፡ገሪቱ የኢኮኖም ዘርፍ ከግብርና ወደ ኢንዱስትሪና የአገልግሎት ዘርፍ እየተቀየረ ሲመጣ የግብር አከፋፈልና አሰባሰብ ሕግጋቶችና ደንቦችም በሚታይና ጉል በሚባል መንገድ ተቀይረዋል። የግብር አከፋፈሉና አሰባሰቡ “ባላዊ” ከመሆን አልፎ “ዘመናዊ” እየመሰለ ለመምጣቱ ሌት ተቀን የሚማረረውን የነጋዴ ማበረሰብ ማነጋገሩ ብቻ በቂ ነው።

የዚህ ጽፍ ዓላማ የግብር ሕጉ ላይ ትችት ለመሰንዘርና የገዥው ፓርቲ የግብር ፖሊሲ በገሪቱ ኢኮኖሚና ማበራዊ ኑሮ ላይ እያስከተለ ያለውን ጉዳት ለመጠቆም የታሰበ ባለመሆኑወደፊት ጊዜና ድል ሲኖር ጸፊው እንደ አንድ የግብር ባለሙያ አስተያያቶቹን በነዚህ ጉዳዮች ላይ ይሰጣል። የዚህ ጽፍ ዓላማ የኢትዮጵያ ገቢዎችና የጉምሩክ ባለሥልጣን በየክፍለ ከተማው በከፈታቸውሕፈት ቤቶቹ በግብር ከፋዩ ማበረሰብ ላይ የሚፈጽመውን ማጉላላትና “በደል” በመጠቆም የባለሥልጣ የሚመለከታቸው ሹማምንት አስፈላጊውን ማሻሻል እንዲያደርጉ ታክስ ከፋዩንም ከመጉላላትና ከሙሰኞች እንዲታደጉት ለማሳሰብ ነው።

አግባብ ባልሆኑራሮችና ውጣ ውረዶች በየመንግት መርያ ቤቱ በነጋዴው ማበረሰብ ላይ ከፍተኛ መጉላላትና በደል እየደረስ ነው። ይህ በደል ሰሚ በማጣቱም ከዚህ በደልና መጉላላትም ለማምለጥ ብዙዎች ለሙስና እየተጋለጡ ለመሆናቸው ነጋሪ የሚያስፈልገው አይመስለኝም፡፡ ይህን በደል “ሞላሽ” አራር ግን ለማሻሻል ሙከራ እየተደረገ ለሆኑ የሚታይ ምንም ነገር የለም፡፡ በተለይም በየክፍለ ከተማው ያሉ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን መሪያ ቤቶች በጣም ጥቂት ከሚባሉ ራተኞች በስተቀር አብዛኞቹ ባለጉዳይ ለማስተናገድም ሆነ መውጫ ቀዳዳው ጠፍቶት ለሚመጣ ግብር ከፋይ መፍትሔ ለመስጠት ብቃትም ሆነ ፍላጎት የሌላቸው ለመሆኑ በእነዚህ ጽሕፈት ቤቶች የሚጉላላው ባለጉዳይ ቋሚ ምስክር ነው፡፡

ለዚህ ጽፍ ምክንያት የሆነኝ በተለይ በቦሌ ክፍለ ከተማ የሚገኘው የገቢዎችና ጉምሩክ ባለልጣን ነው፡፡ በርካታ የገሬው ሰው የሚገምተው ቦሌ ክፍለ ከተማ በብዙ ሁኔታዎች ኢትዮጵያ ውስጥ “የተሻለ” የተባለ ክፍለ ከተማ ነው፡፡ ከዚህ የተሻለ ተብሎ ከሚታበው ክፍለ ከተማ ውስጥ በየመንግት መሪያ ቤቶች ያሉት አራሮች ፍም ግዴለሽነት የሚታይባቸው ብቃት ያላቸው ራተኞችና አስተዳዳሪዎች የሌሉበት መሆኑን ለተገዘበ ሰው በተለይም በዚሕፈት ቤት በግብር ከፋዩ ማኅበረሰብ ላይ የሚደርሰውን ግፍና መጉላላት ላጤ ሰው በሌሎች ክፍላተ ከተች ችግሩ የባሰ መሆኑን በቀላሉ ይረዳል።

የቦው የጉምሩክ ባለሥልጣን ቢሮ በተንጣለለ ፎቅ በአምስቱም ወለሎች (ፎቆች) ቢሮ አለው፡፡ነዚህ ቢዎችም በርካታ ራተኞች አሉ፡፡ ሆኖም ግብር ለመክፈል የሚመጣውን የንግድ ቃድ ለመመለስ የሚመጣውንም ሆነ ከግብር ክፍያ ጋር በተያያ በጽሕፈት ቤቱ የሚመጡ ሰዎችን የሚያስተናግዱት ከስት ሰዎች አይበል፡፡ “ንግድ ቃዴን ለመመለስ ሲያመላልሱኝ ስምንት ወር ፈጀብኝ ሁለት ዓመት ፈጀብኝ. . .” ወዘተ. የሚሉ አቤቱተኞች መስማትና “እኔ ምን ላድርግህ? እና ምን ላድርግሽ? የራስህ/የራሽ ጉዳይ. . .” የሚሉ የቢሮ ራተኞች መስማት በጣም የተለመደ መሆኑን በርካታ ብሶተኞች ለዚህ ጸሐፊ ገልጸዋል። ብዙዎች ከክፍለ ከተማው ከዳ ነ መሆናቸውን ማረጋገጫ (Clearance) ለማግኘት የፈጀባቸውን ጊዜና በዚህም የተነሳ በስሜታቸውራቸውና በገንዘባቸው ላይ የሚደርሰውን ጉዳት በምሬት ሲናገሩ መስማት ልብ ይሰብራል። በአንድ ወቅት በዚሁ ባለሥልጣን ቢሮ በልፍ ለመስተናገድ የሚጠብ ወደ 300 የሚሆዎች ያስተናግድ የነበረው አንድ ሰው ብቻ ነበር፡፡ “እንደውልላቸኋለን ከ15 ቀናት በኋላ ኑ. . .” ወዘተ. እየተባሉ የተባሉት ሳይደረግላቸው የቀሩና መልስ ለማግኘት ጊዜና ጫማ የጨረሱ ግብር ከፋዮች ቁጥር በመቶዎች የሚቆጠሩ ናቸው፡፡

ነዚህ ግብር ከፋዮች ላይ የሚደርሰው ግፍና መጉላላት ተመልካች ያጣ መሆኑ ገሪቱ በመልካም አስተዳድር ጦት ከፍተኛ ችግር ውስጥ እንዳለች ናሙና የሆ ችግሩ ምን ያል ጥልቅና ሰፊ እንደሆነም በግልጽ ያሳያል፡፡ ለአዲስና ለ‹‹ዘመናዊ›› የግብር አከፋልት ገራችን ገና አዲስ ነች ተብሎ ቢታመንም እንኳን በዚህ ዘርፍ ልምድ ካላቸው ከበርካታ ገሮች ትምህርት መውሰድና ችግሮችን መቅረፍ ግብር ከፋዩንም በሚገባ ማስተናገድ የሚቻልበትን አራርና መመርያ መዘርጋት አስቸጋሪ አይደለም፡፡ ፈረንጆቹ እንደሚሉት ጎማውን እንደገና መፍጠር አያስፈልግም፡፡ ጎማው የተፈጠረ በመሆኑ ላፊነት ካለበት ክፍል የሚጠበቀው ጎማውን በተሻለ ሁኔታ ለማሽከርከር ልምድ መውሰድ ብቻ ነው፡፡ ለዚህ ግን ግድ የሚሰጠው አስተዳር ወይም የባለሥልጣን መሪያ ቤት ያስፈልጋል። የገሪቱ ኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት እየሆነ የመጣው የንግዱ ብረተሰብ በተጉላላና በደል በደረሰበት ቁጥር ተጨማሪ ሥራ የመፍጠር መዋዋዩን በአገሩ ላይ የማፍሰስ የንግድ ተቋሙን የማስፋፍት ፍላጎት እየደበዘዘ ይመጣል፡፡ የአዳዲስ ነጋዴዎችንም ፍላጎት ይሰብራል።

በቦሌ ክፍለ ከተማ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን መግቢያ በር ላይ በየወለሉ ባሉ ቢሮዎ ምን ዓይነት ግልጋሎት እንደሚሰጥ የተዘረዘረ ቢሆንም የአብዛኞቹ “ቡድኖች ሥራ” የምርመራና የማጣራት እንጂ በቀጥታ የግብር ከፋዩን ጉዳይ በማስተናገድ መፍትሔ ለመፈለግ የተዘጋጁ አይመስሉም፡፡ ግብር ከፋዩ በተቀላጠፈ ሁኔታ ካልተስተናገደ በመሪያ ላይ ከፍተኛ ጫና እየፈጠረ እንደሚመጣ (አሁንም እንደመጣ) በሠራተኞቹም ሆነ በአስተዳዳሪዎቹ ከግምት ውስጥ የገባ አይመስልም፡፡ ይህ ጸሐፊ እንዳስተዋለው የጉምሩክ ራተኞች (አስተዳዳሪዎቹን ጨምሮ) የድሮ ባላባት ግብር ከፋዩ ደግሞ ጭሰኛ የመለበት ግንኙነት ነው ያላቸው። የባለሥልጣኑ መሪያ ቤት ራተኞች ግብር ከፋዩ ደመወዝ ከፋያቸውና አስተዳዳሪያቸው መሆኑን የሚያውቁም አይመስሉም፡፡ ለነገሩ ይህ ኢትዮጵያ ስጥ በበርካታ የመንግት መሪያ ቤቶች የሚታይ ችግር ነው፡፡ ግብር ከፋዩ ደመወዝ ከፍሎ በሚያስተዳድራቸው የመንግራተኞች ምንም ልጣንም ሆነ መብት የለውም። ጉዳይ ለማስፈጸም ሁሌም መለ መለማማጥ ግፋ ካለ ጉቦ መክፍል አለበት። ስንት ቤተሰብ የሚያስተዳድሩ አባወራዎችና እማወራዎች ስንት ንግድ ተቋም የሚመሩ ዜጎች ብቃት በሌላቸውና ግለሽ በሆኑ የመንግራተኞች ሲዋከቡ ሲመነጫጨቁና ሲዋረዱ ማየት እጅግ ያሳዝናል።

ገዥው ፓርቲ በተደጋጋሚ መልካም አስተዳደር እንደሌለና ሙስና እንደተንራፋ “በተሃድሶ” ነገሮችን እንድሚያስተካክልና እንደሚለውጥ ሲምልና ሲገዘት ብንሰማም በተግባር ግን የምናየው ነገር ተገቢና አስፈላጊ ጥያቄ የሚያነሱ ዜጎችን ዝም ለማሰኘት የጉልበት ርምጃ መውሰድ ነው። በየመንግት መሪያ ቤት በዜጎች ላይ የሚደርሰው መጉላላት በደልና ግፍ ለማንም ሚስጥር አይደለም፡፡ ርማት ለመውሰድ ግን ግድ የሰጠው ክፍል እንደሌለ ነው ልንመሰክር የምንችለው። ዜጎች ደም እንባ የሚያለቅሱበት የቦሌው ክፍለ ከተማ የገቢዎችና  ጉምሩክ ባለልጣን መሥሪያ ቤት ብቻ እንዳልሆነ መናገር አያሻም፡፡ ለቀባሪው ማርዳት ነው የሚሆነው፡፡ በበርካታ መሥሪያ ቤቶች ብቃት የሌላቸው ሰዎች በዘመድና በፖለቲካ ታማኝነት ብቻ ተመው ሕዝብን እንድሚያጉላሉ በጉቦ የዜጎችን ኪስ እንደሚያራቁቱ ለማንም ባለሥልጣን መንገር የሚያስፈልግ አይመስለኝም፡፡ ይህ አፍንጫቸው ር እየተደረገ ያለና አንዳንዴም በሽርክና ተጠቃሚ የሆኑበት ነው። ታ አንድን ክፍለ ከተማ ያውም እንደ ቦሌ ዓይነት ክፍለ ከተማን የመንግሥት መሪያ ቤቶች ማስተካከ ያልቻለ ይልገሪቱን የተሳሰበ ችግር በብቃት እንዴት ሊፈታ ይችላል?

ከአዘጋጁ፡- ጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ ሲሆን፣ ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው [email protected]  ማግኘት ይቻላል፡፡

 

 

 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ለፋይናንስ ዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የማፍራት የቤት ሥራን የማቃለል ጅማሮ

የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እያደገ ለመሆኑ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ  የግል...

የምድር ባቡርን የሚያነቃቃው የመንግሥት ውሳኔ

በኢትዮጵያ ወደብ አልባነት ላይ የተደመረውን የሎጀስቲክስ ችግር ለመፍታት ግዙፍ...

የፓርላማ አባላት ስለሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ግልጽ መረጃ የለንም አሉ

‹‹ሕወሓትን ለፍረጃ አብቅተውት የነበሩ ጉዳዮች በአብዛኛው መልክ ይዘዋል›› ሬድዋን...