ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ አዲሱ ካቢኔያቸውን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቅርበው በሙሉ ድምፅ ፀደቀላቸው፡፡ ባሉበት የቀጠሉና አዳዲስ የካቢኔ አባላት የሚከተሉት ናቸው፡፡
ባሉበት የቀጠሉ
- አቶ ደመቀ መኮንን፦ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር
- አቶ ሲራጅ ፈጌሳ፦ የመከላከያ ሚኒስትር
- አቶ ካሳ ተክለብርሃን፦ የፌዴራል ጉዳዮችና አርብቶ አደር አካባቢ ልማት ሚኒስትር
- ዶክተር ደብረጽዮን ገብረ ሚካኤል፦ የመገናኛና ኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ሚኒስትር
- አቶ አህመድ አብተው፦ የኢንዱስትሪ ሚኒስትር
- አቶ አብዱልፈታህ አብዱላሂ፦ የሠራተኛና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር
- ዶክተር ይናገር ደሴ፦ የብሔራዊ ፕላን ኮሚሽን ኮሚሽነር
- አቶ ጌታቸው አምባዬ፦ የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ
- አቶ አስመላሽ ወልደሥላሴ
፦ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግሥት ዋና ተጠሪ ሚኒስትር
አዲስ የካቢኔ አባላት
- ዶክተር ወርቅነህ ገበየሁ፦ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር
- አቶ ታገሰ ጫፎ፦ የፐብሊክ ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ሚኒስትር
- ዶክተር አብረሃም ተከስተ፦ የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስትር
- ዶክተር በቀለ ጉላዶ፦ የንግድ ሚኒስትር
- ፕሮፌሰር ፍቃዱ በየነ፦ የእንሰሳትና የዓሳ ሀብት ልማት ሚኒስትር
- ዶክተር ኢያሱ አብረሃ፦ የእርሻና ተፈጥሮ ሀብት ሚኒስትር
- ዶክተር ኢንጂነር ጌታሁን መኩሪያ፦ የሳይንስና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር
- አቶ አህመድ ሺዴ፦ የትራንስፖርት ሚኒስትር
- ዶክተር አምባቸው መኮንን፦ የከተማ ልማትና ቤቶች ሚኒስትር
- ኢንጂነር አይሻ መሐመድ፦ የኮንስትራክሽን ሚኒስትር
- ዶክተር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ፦ የውኃ፣ መስኖና ኤሌክትሪክ ሚኒስትር
- አቶ ሞቱማ መቃሳ፦ የማዕድን፣ የነዳጅናየ ተፈጥሮ ጋዝ ሚኒስትር
- ዶክተር ገመዶ ዳሌ፦ የአካባቢ ደን ልማትና የአየር ንብረት ለውጥ ሚኒስትር
- ዶክተር ሽፈራው ተክለማርያም፦ የትምህርት ሚኒስትር
- ፕሮፌሰር ይፍሩ ብርሃነ፦ የጤና ጥበቃ ሚኒስትር
- ዶክተር ግርማ አመንቴ፦ የመንግሥት የልማት ድርጅቶች ሚኒስትር
- ዶክተር ሒሩት ወልደማርያም፦ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር
- ወ/ሮ ደሚቱ ሃምቢሳ፦ የሴቶችና ሕፃናት ጉዳይ ሚኒስትር
- አቶ ርስቱ ይርዳው፦ የወጣቶችና ስፖርት ሚኒስትር
- አቶ ከበደ ጫኔ፦ የገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ኃላፊ ሚኒስትር
- ዶክተር ነገሪ ሌንጮ፦ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ሚኒስትር
በተጨማሪም ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ለተለያዩ ኃላፊዎች በሚኒስትር ደረጃ ሹመት ሰጥተዋል። በዚህም መሠረት፦
- አቶ ሽፈራው ሽጉጤ፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ማዕከል ዋና አስተባባሪ
- አቶ አብዱልአዚዝ መሐመድ፣ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል የፖለቲካ ፓርቲዎችና ሲቪክ ማኅበራት ጉዳዮች አስተባባሪ
- አቶ ተፈራ ደርበው፣ በዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል የገጠር ዘርፍ አስተባባሪ
- ወ/ሮ ፈትለወርቅ ገብረ እግዚአብሔር፣ በዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል የከተማ ዘርፍ አስተባባሪ በማድረግ የሚኒስትር ማዕረግ ሹመት መስጠታቸው ታውቋል።