Sunday, June 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊበወረዳ ሥራ አስፈጻሚና በፖሊስ መኮንኖች ግድያ ግብረ አበር የተባሉ 33 ግለሰቦች ተከሰሱ

በወረዳ ሥራ አስፈጻሚና በፖሊስ መኮንኖች ግድያ ግብረ አበር የተባሉ 33 ግለሰቦች ተከሰሱ

ቀን:

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ ሃና ማርያም አካባቢ በሚገኘውና ‹‹ቀርሳ ኮንቶማ›› በመባል በሚታወቀው ሥፍራ፣ የወረዳውን ሥራ አስፈጻሚና ሁለት የፖሊስ መኮንኖችን በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገደሉ ግብረ አበር ነበሩ የተባሉ 33 ግለሰቦች ጥቅምት 3 ቀን 2009 ዓ.ም. ክስ ተመሠረተባቸው፡፡

ከሰነድ አልባ (ጨረቃ) ቤት ግንባታ ጋር በተያያዘ ሰኔ 22 ቀን 2008 ዓ.ም. ከረፋዱ 5፡00 ሰዓት አካባቢ በነዋሪዎቹና ፀጥታ አስከባሪዎች መካከል ተፈጥሮ በነበረው ግጭት፣ የወረዳ አንድ ሥራ አስፈጻሚ የነበሩት አቶ ታሪክ ፍቅሬና በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምርያ የለቡ ፖሊስ ጣቢያ ሽፍት ኃላፊዎች የነበሩት ኢንስፔክተር ሚካኤል ሽፈራውና ረዳት ኢንስፔክተር ተስፋዬ ባህሩ በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገደሉ፣ ተከሳሾቹ ግብረ አበሮች እንደነበሩ የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ያቀረበው ክስ ያስረዳል፡፡

ተከሳሾቹ ግብረ አበሮች በመሆን የወንጀል ሕግ አንቀጽ 539ን በመተላለፍ የሰው ሕይወት እንዲያልፍ ማድረጋቸውን ክሱ ያስረዳል፡፡

የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ክሱን ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሦስተኛ ወንጀል ችሎት ያቀረበ ሲሆን፣ ፍርድ ቤቱም ክሱን ለተከሳሾቹ በመስጠት በክሱ ላይ መቃወሚያ ካላቸው ለመስማት ለጥቅምት 16 ቀን 2009 ዓ.ም. እንዲያቀርቡ ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡  

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

አወዛጋቢው የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ጉዳይ

በኢትዮጵያ የሕገ መንግሥት ማሻሻል ጉዳይ ከፍተኛ የፖለቲካ ውዝግብ የሚቀሰቀስበት...

 መፍትሔ  ያላዘለው  የጎዳና  መደብሮችን  ማፍረስ

በአበበ ፍቅር ያለፉት ስድስት ዓመታት በርካቶች በግጭቶችና በመፈናቀሎች በከፍተኛ ሁኔታ...

የተናደው ከቀደምቱ አንዱ የነበረው የአዲስ አበባ ታሪካዊ ሕንፃ

ዳግማዊ አፄ ምኒልክ በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ መናገሻ ከተማቸውን...

የአከርካሪ አጥንት ሕክምናን ከፍ ያደረገው ‘ካይሮፕራክቲክ’

በአፍሪካ ከጀርባ ሕመም ጋር በተያያዘ በርካታ ሰዎች ለከፍተኛ የአካል...