የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሕግ ፍትህ አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ፣ ኦሮሚያ በአዲስ አበባ ላይ ባላት ልዩ ጥቅም ለመወሰን በተረቀቀው አዋጅ ላይ ሊያደርገው የነበረውን ሕዝባዊ ውይይት ለሌላ ጊዜ አስተላለፈ፡፡
ውይይቱ ከተጀመረ በኋላ ተቋርጦ ለሌላ ጊዜ የተላለፈው በውይይቱ የተገኙ የኦሮሞ ተወላጆችና የክልሉ አመራሮች፣ የክልሉ ሰላም ባልተረጋጋበት ሁኔታ በልዩ ጥቅም ጉዳይ ላይ ተረጋግተን መወያየት አንችልም በማለት ባነሱት ሐሳብ ምክንያት ነው፡፡
ውይይቱ ሊካሄድ የነበረው በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አዳራሽ ነበር፡፡