Thursday, September 21, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትመኳንንትና መሠረት የቤጂንግ ማራቶንን አሸነፉ

መኳንንትና መሠረት የቤጂንግ ማራቶንን አሸነፉ

ቀን:

ኢትዮጵያውያኑ መኳንንት አየነውና መሠረት መንግሥቱ 36ኛውን የቤጂንግ ማራቶን በወንዶችና በሴቶች ምድብ አሸነፉ፡፡

ቅዳሜ መስከረም 7 ቀን 2009 ዓ.ም. በተካሄደውና በኢንተርናሽናል አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማኅበር የወርቅ ደረጃ ባለው የሩጫ ውድድር፣ በሴቶች የ26 ዓመቷ መሠረት የፈጸመችበት 2፡25፡56 ፈጣኗ ሯጭ አሰኝቷታል፡፡ መሠረትና ተከትላ ሁለተኛ የወጣችው መልካም ግዛው ስትሆን፣ ሰሜን ኮርያዊቷ ጆ ኡን ኦኬ ሦስተኛ ሆናለች፡፡

መሠረት በዓምናው የፓሪስ ማራቶን የራሷን ጊዜ በስድስት ደቂቃዎች በማሻሻል 2፡23፡26 መግባቷ የሚታወስ ሲሆን፣ ባለፈው ቅዳሜ የገባችበት ሰዓት ሁለተኛዋ ምርጥ ጊዜዋ መሆኑን የዓለም አቀፉ ፌዴሬሽን ድረ ገጽ ዘግቧል፡፡

በወንዶች ምድብ የተወዳደረው መኳንንት በአራት ዓመት የማራቶን ተወዳዳሪነቱ ለመጀመሪያ ጊዜ በቤጂንግ ድል የተቀዳጀበት ነው፡፡ የ24 ዓመቱ መኳንንት ባሸናፊነት የፈጸመበት 2፡11፡09 ባንፃራዊ መልኩ ከሴቶቹ ዝግ ያለ መሆኑ ተነግሯል፡፡ ፈየራ ገመዳ (2፡11፡30) እና መስፍን ተሾመ (2፡11፡56) ሁለተኛና ሦስተኛ ወጥተዋል፡፡ ሦስቱም ኢትዮጵያውያን የሽልማት ሠገነቱን ተቆጣጥረውታል፡፡ በቤጂንግ ማራቶን 30,000 ሯጮች መወዳደራቸው ታውቋል፡፡  

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ኮሚሽን ሪፖርት ምን ይዟል?

ለአሜሪካ ድምፅ አማርኛ ዝግጅት የስልክ አስተያየት የሰጡ አንድ የደንበጫ...

መንግሥት በአማራ ክልል ለወደሙ የአበባ እርሻዎች ድጋፍ እንዲያደርግ ተጠየቀ

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአማራ ክልል የተፈጠረው ግጭትና አለመረጋጋት በቢዝነስ...

አምናና ዘንድሮ!

እነሆ መስከረም ጠብቶ በአዲስ መንፈስ ተሞልተን መንገድ ጀምረናል። ‹‹አዲስ...