Sunday, June 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊየቁጠባ ቤቶች ኢንተርፕራይዝ በሙስና ተሳትፈዋል ያላቸውን አመራሮች ከሥራ አገደ

የቁጠባ ቤቶች ኢንተርፕራይዝ በሙስና ተሳትፈዋል ያላቸውን አመራሮች ከሥራ አገደ

ቀን:

 የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቁጠባ ቤቶች ኢንተርፕራይዝ ከኅብረተሰቡ የሚደርሱትን ጥቆማዎች መሠረት በማድረግ  ባደረገው ልዩ ክትትልና ምርመራ፣ ሦስት ከፍተኛ አመራሮችና 15 ፈጻሚዎች በሙስና መሳተፋቸውን በማረጋገጡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቁጠባ ቤቶች ኢንተርፕራይዝ ከኅብረተሰቡ የሚደርሱትን ጥቆማዎች መሠረት በማድረግ ከኃላፊነትና ከሥራ ማገዱን አስታወቀ፡፡

ከተቋቋመ ሦስት ዓመታትን ያስቆጠረው ኢንተርፕራይዙ ከኅብረተሰቡ የመልካም አስተዳደር ዕጦትንና ብልሹ አሠራሮችን የሚመለከቱ ጥቆማዎችን መሠረት በማድረግ ኮሚቴ ማቋቋሙን አስታውቋል፡፡ ኮሚቴው ላለፉት አምስት ወራት ባደረገው ክትትልና ማጣራት፣ አመራሮቹና ሥራ ፈጻሚዎቹ ከሥራ ተቋራጮች ምልመላ፣ ሥምሪት፣ ከአማካሪ መሐንዲሶች የጨረታ ሒደት፣ ከዋና ዋና ግዢዎች አፈጻጸም፣ ከግብዓት አቅርቦትና ሥርጭት ጋር በተያያዘ፣ የሙስና ተግባራት መፈጸማቸውን ማረጋገጡን የኢንተርፕራይዙ የኮሙዩኒኬሽን የሥራ ሒደት መሪ አቶ ዮሐንስ ዓባይነህ ለሪፖርተር አስረድተዋል፡፡

ኢንተርፕራይዙ በተደጋጋሚ ከኅብረተሰቡ በተለይ በጨረታ ከሚሳተፉ ኮንትራክተሮች፣ አማካሪ መሐንዲሶች፣ ከጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች የሚመጣውን ቅሬታና አቤቱታ መመርመሩን አቶ ዮሐንስ ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም ኮሚቴው ከሕዝቡ ያገኘው ጥቆማ ትክክል ሆኖ ስላገኘው ሦስት አመራሮችና 15 ፈጻሚዎችን ከመስከረም 1 ቀን 2009 ዓ.ም. ጀምሮ ከኃላፊነትና ከሥራ በማገድ፣ የማጥራት ሥራ እያከናወነ መሆኑንም አክለዋል፡፡

ማን በምን ደረጃ ችግሩን እንደፈጸመ ተጣርቶ እንደተጠናቀቀ በሕግ የሚጠየቀውን በሕግ፣ በዲሲፕሊን ኮሚቴ የሚጠየቀውን በዲሲፕሊን ኮሚቴ እንዲጠየቅ እንደሚደረግ ገልጸዋል፡፡ ከዋና ዋና ግዢዎች፣ ከኮንትራክተር ምልመላና መረጣ፣ ከአማካሪ ጨረታ ሒደት፣ ከጥቃቅንና አነስተኛ ድርጅቶች አመጣጥ፣ ከሥራ ሥምሪትና የገበያ ትስስር ጋር በተያያዘ ከፍተኛ ሙስና ተፈጽሟል የሚል ግምት መኖሩን ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ የኢንተርፕራይዙ ሠራተኞች ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

አወዛጋቢው የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ጉዳይ

በኢትዮጵያ የሕገ መንግሥት ማሻሻል ጉዳይ ከፍተኛ የፖለቲካ ውዝግብ የሚቀሰቀስበት...

 መፍትሔ  ያላዘለው  የጎዳና  መደብሮችን  ማፍረስ

በአበበ ፍቅር ያለፉት ስድስት ዓመታት በርካቶች በግጭቶችና በመፈናቀሎች በከፍተኛ ሁኔታ...

የተናደው ከቀደምቱ አንዱ የነበረው የአዲስ አበባ ታሪካዊ ሕንፃ

ዳግማዊ አፄ ምኒልክ በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ መናገሻ ከተማቸውን...

የአከርካሪ አጥንት ሕክምናን ከፍ ያደረገው ‘ካይሮፕራክቲክ’

በአፍሪካ ከጀርባ ሕመም ጋር በተያያዘ በርካታ ሰዎች ለከፍተኛ የአካል...