Monday, May 29, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናበእነ አቶ በቀለ ገርባ የክስ መዝገብ ላይ በምስክርነት የተጠሩት የኦሮሚያ ክልል የሥራ...

በእነ አቶ በቀለ ገርባ የክስ መዝገብ ላይ በምስክርነት የተጠሩት የኦሮሚያ ክልል የሥራ ኃላፊዎች ተለዋጭ ቀን እንዲሰጣቸው ኦሕዴድ ጠየቀ

ቀን:

በእነ በቀለ ገርባ የክስ መዝገብ ለተከሰሱ 22 ሰዎች የመከላከያ ምስክር ሆነው እንዲቀርቡ መጥሪያ የደረሳቸው የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ለማ መገርሳ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አቶ አባዱላ ገመዳ፣ የኦሮሞ ሕዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦሕዴድ) ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ዓቢይ አህመድና (/) የለገዳዲ ከተማ ከንቲባ / ጫልቱ ሳኒ በተጠሩበት ቀን ለምስክርነት መቅረብ ስለማይችሉ ተለዋጭ ቀን እንዲሰጣቸው የኦሕዴድ ጽሕፈት ቤት ፍርድ ቤቱን በአክብሮት በደብዳቤ ጠየቀ።

ጽሕፈት ቤቱ ተለዋጭ ቀጠሮ እንዲሰጣቸው የጠየቀበት ምክንያት ለምስክርነት የተጠሩት የሥራ ኃላፊዎች በአገራዊ ጉዳይ ላይ ውይይት እያደረጉ ነው በማለት ነው።

በተመሳሳይ ለዚሁ የክስ መዝገብ በምስክርነት የተጠሩት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ በጽሕፈት ቤታቸው በኩል በሥራ መደራረብ ምክንያት መገኘት እንዳልቻሉ ማስታወቃቸው የሚታወስ ነው።

 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የመስቀል አደባባይ የመግቢያ ክፍያ ለምን?

ወጣቶች፣ ሕፃናትና አረጋውያን ሳይቀሩ መንፈሳቸውን የሚያድሱበት እንዲሁም ሐሳባቸውን በነፃነት...

በሕገ መንግሥቱ የተዋቀረው ‹‹የብሔር ፖለቲካ›› እና ‹‹ሥርዓቱ›› ያስከተለው መዘዝና መፍትሔው

(ክፍል አራት) በዓቢዩ ብርሌ (ጌራ) ባለፈው ጽሑፌ (በክፍል ሦስት) አሁን ያለው...

የኢትዮጵያ ኅብረተሰብና የመንግሥት መሪ ምሥል

በበቀለ ሹሜ በ2015 ዓ.ም. መጋቢት ወር ውስጥ ይመስለኛል በ‹ሸገር ካፌ›...

ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ ያደረገው አዋጅ የፍትሐዊነት ጥያቄ አስነሳ

በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ስምንት ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ በማድረግ ተቋማዊና...