- Advertisement -

በፋይናንስ ዘርፉ ላይ ያተኮረ ጉባዔ ሊካሄድ ነው

በኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፍ ውስጥ ባሉ ዕድሎችና ተግዳሮቶች ላይ የሚመክር ጉባዔ በአዲስ አበባ ሊካሄድ ነው፡፡

ጉባዔው ዓመታዊ የምሥራቅ አፍሪካ የፋይናንስ ጉባዔ ተብሎ የሚጠራ ሲሆን፣ ትኩረቱን በኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፍ ላይ ያደረገ ነው፡፡ የመጀመሪያው ጉባዔ በታኅሳስ 2009 ዓ.ም. በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይካሄዳል፡፡ ስብሰባውን በማዘጋጀት ላይ የሚገኘው አይ ካፒታል አፍሪካ ኢንስቲትዩት ከመንግሥት የፋይናንስ ተቋማት ኤጀንሲ፣ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲና ከጂማ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ነው፡፡

የአይ ካፒታል ኢንስቲትዩት ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ገመቹ ዋቅቶላ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን በሒደት ላይ የምትገኝ አገር እንደመሆኗ የፋይናንስ ዘርፉን ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት ማድረጓ የማይቀር ጉዳይ ነው፡፡ በመጪው ታኅሳስ ወር የሚካሄደው የፋይናንስ ጉባዔ የኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለመሆን ዝግጁ ነው ወይ? የሚለውን እንደሚመለከት ዶ/ር ገመቹ ተናግረዋል፡፡

የፋይናንስ ዘርፉ ለውጭ ኢንቨስትመንት ክፍት ከመሆኑ በፊት ሊወሰዱ በሚገባቸው ዕርምጃዎች ዙሪያ የፋይናንስ ምሁራን ጥናታዊ ጽሑፍ ያቀርባሉ፡፡ አይ ካፒታል አፍሪካ ኢንስቲትዩት በኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፍ የዳሰሳ ጥናት ማካሄዱን የገለጹት ዶ/ር ገመቹ፣ ዘርፉ የተለያዩ ችግሮች እንደሚታዩበት ተናግረዋል፡፡ ባለፉት ዓመታት በርካታ የግል ባንክና ኢንሹራንስ ኩባንያዎች ቢከፈቱም አሁንም ከፍተኛ ቁጥር ያለው የኅብረተሰብ ክፍል በፋይናንስ አገልግሎት ተጠቃሚ እንዳልሆነ የገለጹት ዶ/ር ገመቹ፣ ይህን የኅብረተሰብ ክፍል ወደ ዘርፉ ለማምጣት ምን መደረግ አለበት በሚለው ላይ ውይይት እንደሚደረግ አስረድተዋል፡፡

በኢትዮጵያ ከባንክ ብድር ማግኘት ከፍተኛ ውጣ ውረድ የሚጠይቅ ሒደት እንዳለው የገለጹት ዶ/ር ገመቹ፣ ባንኮች የሚከተሉዋቸው አሠራሮች የተለመዱ መሆናቸውን ጠቅሰው ከተለመዱት ውጪ አዳዲስ የባንክ አገልግሎቶችን መጀመር እንደሚያስፈልግ አክለዋል፡፡

‹‹ባንኮች በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂዎች ላይ ከፍተኛ ኢንቨስትመንት ያደርጋሉ፡፡ ይሁን እንጂ የገዙዋቸውን ቴክኖሎጂዎች ሙሉ በሙሉ እየተጠቀሙባቸው አይደሉም፡፡ ከፍተኛ የሆነ የዕውቀትና የሠለጠነ ሰው ኃይል ውስንነት አለባቸው፤›› ያሉት ዶ/ር ገመቹ፣ ባንኮች ባለው ውስን የባንክ ባለሙያ ምክንያት ባለሙያ እንደሚቀማሙ ጠቁመዋል፡፡ የፋይናንስ ጉባዔው ለሰው ኃይል ልማት፣ ለባንክ ቴክኖሎጂና ለፋይናንስ ሕግና ደንቦች ከፍተኛ ትኩረት እንደሚሰጥ ገልጸዋል፡፡

- Advertisement -

የፋይናንስ ተቋማት መሪዎች፣ ፖሊሲ አውጪዎችና ተቆጣጣሪዎች፣ የፋይናንስ ዘርፍ ተመራማሪዎችና የውጭ ባንኮችና ዓለም አቀፍ የፋይናንስ ተቋማት ተወካዮች የሚካፈሉበት የፓናል ውይይት እንደሚካሄድ ለማወቅ ተችሏል፡፡ አይ ካፒታል ኢንስቲትዩት በመጋቢት 2008 ዓ.ም. የምሥራቅ አፍሪካ የሲሚንቶ፣ ኮንክሪትና ኢነርጂ ጉባዔ በአዲስ አበባ ማዘጋጀቱ ይታወሳል፡፡ 

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

ለከተራና ጥምቀት በዓላት ትኩረት የሚሹት ለኮሪደር ልማት የተቆፋፈሩ መንገዶች

የዘንድሮ የጥምቀት በዓል በተለይ በአዲስ አበባ ለየት ባለ ጥበቃ የሚከበር ስለመሆኑ የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ አስታውቋል፡፡ የደንብ ማስከበር ባለሥልጣንና ሌሎች አካላትም በዓሉ በሰላም...

ኢትዮጵያዊቷ ተማሪ የ2025 የሁዋዌ ዓለም አቀፍ አምባሳደር ሆና ተመረጠች

የሥላሴ ዩኒቨርሲቲ አራተኛ ዓመት የኮምፒዩተር ሳይንስ ተማሪ አሲያ ከሊፋ የሁዋዌ የ2025 የሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር ዓለም አቀፍ አምባሳደሮች አንዷ ሆና ተመረጠች፡፡ ሁዋዌ ከመረጣቸው 12 አምባሳደሮች...

አገልግሎት የማይሰጡና 32 ሚሊዮን ብር ግምት ያላቸው ምግብና የንፅህና መጠበቂያ ምርቶች ተወገዱ

ባለፉት ስድስት ወራት ከ32 ሚሊዮን ብር በላይ ግምታዊ ዋጋ ያላቸው፣ የተበላሹ ምግቦችና የንጽሕና መጠበቂያ ምርቶች መወገዳቸውን፣ የአዲስ አበባ ከተማ ምግብና መድኃኒት አስተዳደር ቁጥጥር ባለሥልጣን...

የቤተሰብ ኃላፊነት የተሸከሙ ሕፃናት

በመማሪያና በለጋ ዕድሜያቸው የቤተሰብ ኃላፊነት ተጭኖባቸው ከትምህርት ገበታ ርቀው የሚቀሩ ሕፃናት በርካታ ናቸው፡፡ በቤተሰብ መበተን፣ ከቀዬ በመፈናቀልና በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ሕፃናትና ታዳጊዎች ሲለምኑ፣ ሶፍትና...

ልሂቅ የምጣኔ ሀብት ባለሙያና ፖለቲከኛ በፍቃዱ ደግፌ (ዶ/ር) ሲታወሱ

የምጣኔ ሀብት (ኢኮኖሚክስ) ዕውቀትን እስከ ሦስተኛ ዲግሪ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል በከፍተኛ ደረጃ ያስተማሩ፣ ያማከሩ ነበሩ፡፡ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የነበራቸው የአገልግሎት ቁርጠኝነት...

በኮዬ ፈጬ ክፍለ ከተማ ጫማ ጠራጊዎች ያለ ደረሰኝ ግብር እየከፈልን ነው አሉ

በሸገር ከተማ ኮዬ ፈጬ ክፍለ ከተማ ወዴሳ ወረዳ በጫማ መጥረግ ሥራ ላይ የተሰማሩ ግለሰቦች ያለ ደረሰኝ በወር 2,700 ብር ግብር በመክፈል ላይ መሆናቸውን ተናገሩ፡፡...

አዳዲስ ጽሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ቀኑን ሙሉ ከዋሉበት የሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ተመልሰው ከባለቤታቸው ጋር እያወጉ ነው]

የምን ስብሰባ ላይ ዋልኩ ነበር ያልከኝ? የሥራ አስፈጻሚ። የምን ሥራ አስፈጻሚ? የገዥው ሥራ አስፈጻሚ። ምን ገጥሟችሁ ነው የተሰበሰባችሁት? ለመረጠን ሕዝብ ቃል የገባናቸውን ተግባራት አፈጻጸም የምንገመግምበት የተለመደ ስብሰባ ነው። የገባችሁት ቃል...

ሕወሓትን አጣብቂኝ ውስጥ የከተተው መመርያ

በሁለት አንጃ ተከፍሎ የእርስ በርስ የቃላት ጦርነት ውስጥ የገባው ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ልዩነቱን ትቶ ወደቀድሞው አንድነቱ በመመለስ የሚጠበቅበትን ጠቅላላ ጉባዔ የማድረግ አልያም...

ባንኮች እየፈጸሙት ያለው አቅርቦትንና ፍላጎትን ያላገናዘበ የውጭ ምንዛሪ ግዥ

የውጭ ምንዛሪ ግብይት በገበያ ዋጋ እንዲገበይ የወጣው ሕግ ተግባራዊ መሆን ከጀመረ ከሰባት ወራት በላይ አስቆጥሯል፡፡ ሕጉ ተግባራዊ በተደረገበት የመጀመርያው ቀን የአንድ ዶላር የምንዛሪ ዋጋ...

አሳረኛው ኑሮ!

የዛሬው ጉዞ ከቦሌ ወደ ፒያሳ ይሆን ዘንድ ግድ ሆኗል፡፡ ለምን? በኑሮ  ምክንያት፡፡ የታክሲ መሠለፊያው ወሬ የነዳጅ ጭማሪውን ተከትሎ ስለሚመጣው ተጨማሪ ታሪፍ ነው፡፡ ‹‹የእኛ ኑሮ...

የግለሰቦች ለመብታቸው ኃላፊነት አለመውሰድ ለአገር ያለው አደጋ

በያሬድ ኃይለመስቀል አንድ የማከብረው ኢኮኖሚስት አንድ መጽሐፍ እንዳነብ መራኝና ማንበብ ጀመርኩኝ። ይህንን መጽሐፍ ሳነበው ከዋናው ሐሳብ ወጣ ብሎ ስለ “የነፃ ተጓዦች ሀተታ” (The Free Rider...

‹‹የብድርና ቁጠባ ኅብረት ሥራ ማኅበራትን ኢኮኖሚያዊ አስተዋጽኦ ማጠናከር ያስፈልጋል›› አቶ ፍፁም አብርሃ፣ የአሚጎስ ብድርና ቁጠባ ኅብረት ሥራ ማኅበር መሥራችና ሥራ አስኪያጅ

አሚጎስ የብድርና ቁጠባ ኅብረት ሥራ ማኅበር ከተመሠረተ አሥራ ሁለት ዓመታት ሆኖታል፡፡ በእነዚህ ዓመታት 8,500 አባላትን ማፍራት ችሏል፡፡ አሚጎስ ስለተመሠረተበት ዓላማ፣ እያከናወናቸው ስለሚገኙ ተግባራት፣ የብድርና...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን