Thursday, June 1, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ፍሬከናፍርለአገሬ ያለኝ ፍቅር ለሥልጣን ካለኝ ፍላጎት የላቀና የጠነከረ ነው።

ለአገሬ ያለኝ ፍቅር ለሥልጣን ካለኝ ፍላጎት የላቀና የጠነከረ ነው።

ቀን:

‹‹ለአገሬ ያለኝ ፍቅር ለሥልጣን ካለኝ ፍላጎት የላቀና የጠነከረ ነው። ለዚህም ነው የፕሬዚዳንታዊ ምርጫውን አሸናፊ ጆርጅ ዊሃን በስልክ እንኳን ደስ ያልዎት ያልኋቸው። በማንኛውም መንገድ ልረዳቸውም ራሴን አዘጋጅቻለሁ። የመርከቧ ካፒቴን ባልሆን እንኳ የመንግሥታችን መርከብ በሰላም እንድትቀዝፍ ጥልቅ ምኞቴ ነው።››

የቀድሞው የላይቤርያ ምክትል ፕሬዝዳንትና ሰሞኑን በተካሄደው ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ በጆርጅ ዊሃ የተሸነፉት ጆሴፍ ቦዓካይ የተናገሩት፡፡ በዳግም ምርጫ ፉክክር ጊዜ ባሰሙት ቅስቀሳዊ ዲስኩር  ‹‹ከአሸናፊነቴ የሚገታኝ አንዳችም አይኖርም›› ያሉት ቦዓካይ  መሸነፋቸውን አሜን ብለው ለመቀበል አላቅማሙም፡፡ እንዲያውም አገሬን የማገለግልበት ሌሎች መንገዶች ይኖሩኛል በማለትም አክለዋል፡፡ ተመራጩ የላይቤሪያ ፕሬዝዳንታዊ ጆርጅ ዊሃ በአንድ ወቅት የፊፋ የዓለም የእግር ኳስ ኮከብ ተጫዋች ሆነው የተመረጡኤሲ ሚላን፣ ፓሪሴን ዠርሜን እና ቼልሲ ክለቦች የተጫወቱት ናቸው፡፡  ዊሃ መንበረ ፕሬዚዳንቱን ከመጀመርያዋ አፍሪካዊት ፕሬዚዳንት ኤለን ጆንሰን ሰርሊፍ  በቀጣዩ ወር ይረከባሉ፡፡

 

 

 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...