Wednesday, March 29, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

ክቡር ሚኒስትሩ አማካሪያቸውን ቢሮ ያስጠሩታል

  • አቤት ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • አሁን የምሰጥህን ዶክመንት በጥንቃቄ እንድትይዘው፡፡
  • ምን ዓይነት ዶክመንት ነው?
  • ይህ ዶክመንት በአሁኑ ወቅት ወሳኝ የሚባል ዶክመንት ነው፡፡
  • ይኼ በእጅዎ የያዙት ዶክመንት ነው?
  • አዎን፡፡
  • በጣም ብዙ ገጽ ነው፣ ሁለተኛው ዙር ሊጀመር ነው እንዴ?
  • የምን ሁለተኛ ዙር ነው?
  • የሙስና ዘመቻው ሁለተኛ ዙር ነዋ፡፡
  • ምንድነው የምትቀባጥረው?
  • የስም ዝርዝሩን ነው እንዴ የያዙት?
  • ሰውዬ በሰላም ነው አድረህ የተነሳኸው?
  • እኔማ ሁለተኛው ክፍል ተጀመረ ብዬ ነው?
  • ምን ይላል ይኼ?
  • ያው በመንግሥትና በሕዝብ ላይ በቢሊዮን የሚቆጠር ጉዳት ያደረሱት ተያዙ ብዬ ነዋ፡፡
  • እነሱማ ያኔ ተያዙ አይደል እንዴ?
  • ዋናዎቹ መቼ ተያዙ?
  • እ. . .
  • ጭፍራዎቹ በቢሊዮን ከዘረፉ ዋናዎቹ እኮ ስንት ነው የዘረፉት እየተባለ ነው የሚወራው፡፡
  • ምን ለማለት ፈልገህ ነው?
  • እኔ እርስዎን ማለቴ አይደለም፡፡
  • እሱም አምሮህ ነበር?
  • ያው መቼም ራስዎ ያሉበትን ሊስት ራስዎ አይዙትም ብዬ ነው፡፡
  • መልዕክት ልታስተላልፍልኝ ፈልገህ ነው?
  • ኧረ በፍፁም ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ለማንኛውም ዶክመንቱን ተቀበለኝ፡፡
  • ምንድንው ግን ዶክመንቱ?
  • መግለጫው ነዋ፡፡
  • የምን መግለጫ?
  • ሰሞኑን ከ15 ቀናት በላይ በራችንን ዘግተን የተገማገምንበትን፡፡
  • ምን ላድርገው ክቡር ሚኒስትር?
  • መግለጫ ምንድነው የሚደረገው?
  • በቲቪና በሬዲዮ ላሠራጨው?
  • አንተ ግን 21ኛው ክፍለ ዘመን ላይ መሆናችንን ረሳኸው?
  • ምን እያሉኝ ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • በዚህ ወቅት ቲቪና ሬዲዮ የሚከታተል አለ?
  • እ. . .
  • አንተ አሁን ለምሳሌ በቲቪ ዜና ታያለህ?
  • ሲኤንኤንና አልጄዚራ ላይ አያለሁ፡፡
  • ስለእነሱ ማን ጠየቀህ?
  • ታዲያ ስለማን ነው የጠየቁኝ?
  • ስለአገራችን ሚዲያዎች ነው የጠየቅኩህ?
  • እነሱንማ አይቻቸውም አላውቅ፡፡
  • ታዲያ አንተ የማታያቸውን ሕዝቡ እንዲያያቸው ትጠብቃለህ?
  • እሱስ እውነትዎን ነው፡፡
  • ስለዚህ አሁን በአስቸኳይ ይለቀቅ፡፡
  • ምን ላይ ነው የሚለቀቀው?
  • ፌስኦፍ ላይ ነዋ፡፡
  • ምን ላይ?
  • በኢንተርኔት ልቀቀው፡፡
  • ፌስቡክ ለማለት ነው?
  • አዎን እሱ ላይ፡፡
  • እሱማ ተዘግቷል ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ማን አባቱ ነው የዘጋው?
  • መንግሥት ነዋ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ለምን ተብሎ?
  • ለአገሪቷ ሰላምና ደኅንነት ሲባል ተዘግቷል፡፡
  • እሱ በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ጊዜ አልነበር እንዴ የተዘጋው?
  • አሁንም ግን ተዘግቷል፡፡
  • እንዴት ግን ሊዘጋ ቻለ?
  • ምናልባት በይፋ ያልታወጀ የአስቸኳይ ጊዜ ላይ እንሆናለና?
  • ለነገሩ ፌስቡክ ሲዘጋ የሚታይበት መንገድ አለ አይደል?
  • ቪፒኤን ማለትዎ ነው?
  • ነው መሰለኝ፡፡
  • ታዲያ በቪፒኤን ተጠቅሜ ፌስቡክ ላይ ልልቀቀው?
  • እህሳ፡፡
  • ይህ ግን ትዝብት ውስጥ አይከተንም?
  • የምን ትዝብት?
  • መንግሥት ራሱ ፌስቡክን ዘግቶት፣ መግለጫውን በፌስቡክ ሲለቅ ነዋ?
  • ምንም ችግር የለውም ዝም ብለህ የታዘብከውን አድርግ፡፡
  • አሁን ግን ዶክተሩን አስታወሱኝ፡፡
  • የትኛውን ዶክተር?
  • ሲጋራ አታጭሱ እያለ የሚመክረውን ነዋ፡፡
  • ቢመክር ምን ችግር አለው?
  • ራሱ ስለሚያጨስ!

[የክቡር ሚኒስትሩ ወዳጅ ሚኒስትር ቢሯቸው ይመጣሉ]

  • እንዲያው አንዳንድ ነገሮች ላይ እንድንመካከር ብዬ ነበር ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምን ዓይነት ነገሮች ላይ?
  • ሕዝቡ እኮ በጉጉት ሲጠብቀን ነበር፡፡
  • ለምንድነው በጉጉት የሚጠብቀን?
  • ያው 17 ቀን ዘግተን ተሰብስበን ከእኛ ትልቅ ነገር ነበር የሚጠብቀው፡፡
  • ታዲያ ከእኛ የሚጠብቀውን ነገር ሰጠን አይደል እንዴ?
  • ምን ሰጠን ክቡር ሚኒስትር?
  • መግለጫ ሰጠን አይደል እንዴ?
  • ችግሩ መግለጫው አይደል እንዴ?
  • ምን ሆነ መግለጫው?
  • ሕዝቡ በመግለጫው መላጫ እያደረገን ነው፡፡
  • ምን እያልክ ነው?
  • መግለጫው በመጽሐፍ መልክ ቢታተም ይሻል ነበር መሰለኝ?
  • ለምን?
  • መብዛቱ ሳያንስ ውስጡ አደናጋሪ ነው፡፡
  • አንተ ከፀረ ሰላም ኃይሎች ጋር ውለሃል ማለት ነው፡፡
  • ለማንኛውም ክቡር ሚኒስትር ሕዝቡ መግለጫውን በሚገባ የተረዳው አልመሰለኝም፡፡
  • ስማ ፓርቲያችን እኮ ሚስጥራዊ ፓርቲ መሆኑን አትርሳ፡፡
  • ምን እያሉ ነው ክቡር ሚኒስትር?
  • ሁሉን ነገር ለሕዝብ ግልጽ የማድረግ ባህል የለውማ፡፡
  • በሌላ በኩል ደግሞ መንግሥት ግልጽ መሆን አለበት እንላለን፡፡
  • መንግሥት ሌላ ፓርቲ ሌላ፡፡
  • በመግለጫው አመራሩ ጥፋተኛ ከሆነ ተጠያቂም መሆን አለበት እያለ ነው ሕዝቡ፡፡
  • አንተ በፓርቲው ማንም ተጠያቂ ሊሆን እንደማይችል አታውቅም እንዴ?
  • መንግሥት ግን ተጠያቂ መሆን አለበት እኮ?
  • ሰውዬ መንግሥት ሌላ፣ ፓርቲ ሌላ አልኩህ እኮ?
  • አሁን ግን እኔንም እያደናገሩኝ ነው፡፡
  • ለምን ተደናገርክ?
  • በመንግሥት ደረጃ ግልጽና ተጠያቂ መሆን አለብን እያልን በፓርቲ ደግሞ ግልጽነትና ተጠያቂነት ባህላችን አይደለም እንላለን፡፡
  • ታዲያ ምን ችግር አለው?
  • ክቡር ሚኒስትር ሕዝቡ በመግለጫው ላይ ተመሥርቶ መላምት እያቀረበ ነው፡፡
  • ሕዝቡ የተለያዩ መላምቶችን ካቀረበ እኛም ግባችንን መተናል ማለት ነው፡፡
  • የእኛ ግብ ምንድነው?
  • ማደናገር!

[ለክቡር ሚኒስትሩ ኢንቨስተር ወዳጃቸው ይደውልላቸዋል]

  • ክቡር ሚኒስትር ያወጣችሁትን መግለጫ አየሁት፡፡
  • እንዴት አገኘኸው?
  • ክቡር ሚኒስትር የእናንተ ነገር እኮ እንቆቅልሽ እየሆነብኝ ነው፡፡
  • ምን እያልክ ነው?
  • እስኪ መጀመርያ አንድ ጥያቄ ይመልሱልኝ?
  • ምንድነው ጥያቄህ?
  • አሁን አገሪቱ ለገባችበት ቀውስ አመራሩ ጥፋተኛ ነው አላችሁ፡፡
  • ትክክል ነው፡፡
  • ታዲያ አመራሩ የታለ የተቀጣው?
  • አንተ ኢትዮጵያዊ አይደለህ እንዴ?
  • ነኝ እንጂ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ታዲያ እኛ በባህላችን ይቅር ባይና ሩህሩህ አይደለንም እንዴ?
  • ይኼ ነው እኮ ችግሩ?
  • እንዴት?
  • ሕዝቡን በልታችሁ ከጨረሳችሁት በኋላ ይቅር ይበለን ስትሉ አታፍሩም?
  • ስማ አንተ ከዳያስፖራዎቹ ጋር ግንኙነት ስላለህ ጨካኝ ሆነሃል፡፡
  • ክቡር ሚኒስትር አሁን የሚሉት ነገር ኢትዮጵያ ውስጥ እንደ ባህል እየተወሰደ ነው፡፡
  • አልገባኝም?
  • ስንቱን ያማረረ ሰው ሞቶ ታሪኩ ሲነበብ ደግ፣ ሩሩህና ቸር ነበሩ ነው የሚባለው፡፡
  • ምን ለማለት ፈልገህ ነው?
  • እናንተም ሕዝቡን አሰቃይታችሁ ስታበቁ ደግ፣ ሩሩህና ቸር ነበራችሁ እንዲባልላችሁ ትፈልጋላችሁ?
  • አንተ ለማንኛውም የለየልህ ተቃዋሚ እየሆንክ ነው፡፡
  • ሌላው ደግሞ መግለጫውን ለምንድነው እንደዚህ አደናጋሪ ያደረጋችሁት?
  • ምኑ ነው ያደናገረህ?
  • አሁን መርህ አልባ ግንኙነት ማለት ምን ማለት ነው?
  • እንደገባህ ነዋ የምትፈታው፡፡
  • ምን ማለት ነው እንደገባህ ፍታው ሲሉ?
  • እንደተጻፈው መርህ አልባ ግንኙነት ማለት ነዋ፡፡
  • ቡድናዊ ትስስርስ ማለት ምንድነው?
  • እሱም የቡድን ትስስር ማለት ነዋ፡፡
  • ኧረ ክቡር ሚኒስትር በዚህ ሕዝብ ላይ አትቀልዱበት?
  • ሰውዬ እንዲያውም ይኼ እስከ ዛሬ ካወጣናቸው መግለጫዎች ግልጽ መግለጫ ነው፡፡
  • እኔ ግን ክቡር ሚኒስትር አንድ ነገር አልደብቅዎትም፡፡
  • ምን?
  • መግለጫውን ለመረዳት አምስት ጊዜ አንብቤዋለሁ፡፡
  • እሺ?
  • ከማንበብ ባለፈ ሦስት ጊዜም አዳምጨዋለሁ፡፡
  • ታዲያ እንዴት  አገኘኸው?
  • ምንም አልገባኝም፡፡
  • እ. . .
  • ሌሎችም ብጠይቅ እነሱም አልገባቸውም፡፡
  • ምን እያልክ ነው?
  • አሁን የቀረኝ አንድ ነገር ብቻ ነው፡፡
  • ምንድነው የቀረህ?
  • መግለጫውን ማስፈታት፡፡
  • የት?
  • ጠንቋይ ቤት!

 

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

የኦሮሞን ሕዝብ ታሪክ አልባ በማድረግ ታሪክ አይሠራም

በኢተፋ ቀጀላ​​  ከዛሬ ሃምሳ ዓመት ወዲህ ከተፈጠሩት የኦሮሞ ድርጅቶች መካከል ከኢጭአት በስተቀር፣...

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንና የመንግሥት ውዝግብ

የጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) መንግሥት ባለፉት አራት ዓመታት...

የኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ሥጋቶች

ዘ ኮንቨርሴሽን ላይ ‹‹What Next for Ethiopia and its...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

‹‹ከኦነግ ሸኔ ጋር ያለውን ግጭት በሰላም ለመፍታት ከፍተኛ ፍላጎት አለን›› ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ

መንግሥት ከ‹‹ኦነግ ሸኔ››ጋር ያለውን ግጭት በሰላም ለመፍታት ከፍተኛ ፍላጎት...

ለፋይናንስ ዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የማፍራት የቤት ሥራን የማቃለል ጅማሮ

የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እያደገ ለመሆኑ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ  የግል...

የምድር ባቡርን የሚያነቃቃው የመንግሥት ውሳኔ

በኢትዮጵያ ወደብ አልባነት ላይ የተደመረውን የሎጀስቲክስ ችግር ለመፍታት ግዙፍ...

የፓርላማ አባላት ስለሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ግልጽ መረጃ የለንም አሉ

‹‹ሕወሓትን ለፍረጃ አብቅተውት የነበሩ ጉዳዮች በአብዛኛው መልክ ይዘዋል›› ሬድዋን...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር ሚኒስትር? እርሶዎማ ቀጠሮ መያዝ አያስፈልግዎትም። ምን ገጠመዎት? እኔማ ምን ይገጥመኛል፣ አንተኑ ልጠይቅህ እንጂ? ምን? እውነት ለመናገር የማየው ነገር አሳስቦኛል። ይንገሩኝ...

[የባለሥልጣኑ ኃላፊ የቴሌኮም ኩባንያዎች የስልክ ቀፎ የመሸጥ ፈቃድ እንዳላቸው ለማረጋገጥ ክቡር ሚኒስትሩ ጋር ደወሉ]

ክቡር ሚኒስትር ዕርምጃ ከመውሰዳችን በፊት አንድ ነገር ለማጣራት ብዬ ነው የደወልኩት። እሺ ምንን በተመለከተ ነው? የቴሌኮም ኩባንያዎችን በተመለከተ ነው። የቴሌኮም ኩባንያዎች ምን? የቴሌኮም ኩባንያዎች የሞባይል ቀፎ እንዲሸጡ በሕግ...

[ክቡር ሚኒስትሩ ተቋቋመ ስለተባለው የሽግግር መንግሥት ከአማካሪያቸው መረጃ እየጠየቁ ነው]

እኛ ሳንፈቅድ እንዴት ሊያቋቁሙ ቻሉ? ስምምነታችን እንደዚያ ነው እንዴ? በስምምነታችን መሠረትማ እኛ ሳንፈቅድ መቋቋም አይችልም። የእኛ ተወካዮችም በአባልነት መካተት አለባቸው። ታዲያ ምን እያደረገ ነው? ስምምነቱን መጣሳቸው...