Friday, December 1, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትየፋጡማ ሮባና የቲኪ ገላና ድልን የሚሠልሰው ማን ነው?

የፋጡማ ሮባና የቲኪ ገላና ድልን የሚሠልሰው ማን ነው?

ቀን:

ኢትዮጵያውያት የሚጠበቁት የሴቶች ማራቶን ውድድር ነሐሴ 8 ቀን 2008 ዓ.ም. ከቀኑ 9፡30 ይደረጋል፡፡ በውድድሩም ትዕግሥት ቱፋ፣ ማሬ ዲባባና ትርፊ ፀጋዬ ይሳተፋሉ፡፡

ለመጀመርያ ጊዜ በኦሊምፒክ የሚሳተፉት አትሌቶች ከፍተኛ ፉክክር እንደሚያደርጉ ይጠበቃል፡፡ ከፍተኛ ልምድ ያላት ማሬ ዲባባና የቅርቦቹ አትሌቶች የሚያደርጉት ውድድር በብዙዎች ዘንድ ተጠባቂ ያደርጋቸዋል፡፡ በተለይ ማሬ እ.ኤ.አ. በ2015 በቻይናዋ ቤጂንግ በተካሄደው የዓለም ሻምፒዮና በማራቶን የወርቅ ሜዳሊያ ያገኘችው ርቀቱን 2 ሰዓት 27 ደቂቃ ከ39 በመግባት ነበር፡፡

 ሌላዋ ተፎካካሪ ትዕግሥት ቱፋ በ2014 ሻንጋይ ማራቶን የራስዋን ሪከርድ ያሰፈረች ሲሆን፣ ውድድሩን 2 ሰዓት ከ21 ደቂቃ ከ52 በመጨረስ ልምድም ያገኘችበት ውድድር ነው፡፡ ለሪዮ ኦሊምፒክ እንድትመረጥ ያስቻላትን ውጤት ያገኘችው በ2015  ለንደን ማራቶን 2 ሰዓት ከ23 ደቂቃ ከ22 በመግባት ማሸነፏ ነው፡፡ አትሌቷ አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ ሴት የረዥም ርቀት አትሌቶች ተስፋ ተጥሎባታል፡፡

ሌላኛዋ አትሌት ትርፊ ፀጋዬ ምርጥ ጊዜዋ ትርፊ 2 ሰዓት ከ20 ደቂቃ ከ18 ሰከንድ በ2014 የበርሊን ማራቶን ላይ ያጠናቀቀችበት ሲሆን፣ የፓሪስና የቶኪዮ የማራቶን አሸናፊ ነበረች፡፡ በዘንድሮ የሪዮ ኦሊምፒክ ላይ የተቻላትን ጥረት አድርጋ ስሟን በኦሊምፒክ ማስፈር እንደምትፈልግ ተናግራለች፡፡

ኢትዮጵያ በኦሊምፒክ ተሳትፎዋ እ.ኤ.አ. በ1996 በአትላንታ ሴቶች ማራቶን ፋጡማ ሮባ 2 ሰዓት ከ26 ደቂቃ ከ05 በመግባት የመጀመርያውን ወርቅ አምጥታለች፡፡ ከዚያ በኋላ በሴቶች ማራቶን በኦሊምፒክ ወርቅ ለማምጣት አራት ኦሊምፒያድ ወስዷል፡፡ በቲኪ ገላና አማካይነት በ2012ቱ የለንደን ኦሊምፒክ ወርቅ ተመዝግቧል፡፡ ከአራት ዓመት በፊት በለንደን ጎዳና ላይ በተደረገው ውድድር ቲኪ ርቀቱን 2 ሰዓት ከ23 ደቂቃ ከ07 በመፈጸም የኦሊምፒክ ሪከርድ መስበሯ ይታወሳል፡፡

በዘንድሮም የሪዮ ኦሊምፒክ ከፋጡማና ቲኪ ቀጥሎ ሦስተኛዋ ኢትዮጵያዊት ባለድል ማን ትሆን?

 

 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የመቃወም ነፃነት ውዝግብ በኢትዮጵያ

ስሟ እንዳይገለጽ የጠየቀችው በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ የሾላ አካባቢ...

የሲሚንቶን እጥረትና ችግር ታሪክ ለማድረግ የተጀመረው አጓጊ ጥረት

በኢትዮጵያ በገበያ ውስጥ ለዓመታት ከፍተኛ ተግዳሮት በመሆን ከሚጠቀሱ ምርቶች...

የብሔር ፖለቲካው ጡዘት የእርስ በርስ ግጭት እንዳያባብስ ጥንቃቄ ይደረግ

በያሲን ባህሩ በሪፖርተር የኅዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ዕትም “እኔ...