- Advertisement -

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከወጣቶች ጋር ሊወያዩ ነው

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ነሐሴ 14 ቀን 2008 ዓ.ም. በሚሊኒየም አዳራሽ ከወጣቶች ጋር ሊወያዩ ነው፡፡

ውይይቱ ከወጣቶች ፖሊሲ ላይ የተቀዱ ዋና ዋና የልማት ስትራቴጂዎችና ፖሊሲዎች፣ እንዲሁም በፕሮግራሞች ውስጥ የወጣቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ምን ደረጃ ላይ ደርሷል? ስኬቶቹ ምንድን ናቸው? ያጋጠሙ ተግዳሮቶች ምን ይመስላሉ? ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ምን መሆን አለባቸው? በሚሉ ጉዳዮች ላይ እንደሚያተኩር ተገልጿል፡፡

የወጣቶችና ስፖርት ሚኒስቴር የወጣቶች ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ አዲሱ አረጋ ማክሰኞ ነሐሴ 3 ቀን 2008 ዓ.ም. በብሔራዊ ሆቴል በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ በውይይቱ ላይ ሦስት ሺሕ ወጣቶች እንደሚሳተፉና ከተሳታፊዎቹም ውስጥ 30 በመቶ የሚሆኑት ሴቶች እንደሚሆኑም ገልጸዋል፡፡

በውይይቱ ላይ ከሁሉም ክልሎችና ከሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች፣ በገጠር፣ በአርብቶ አደርና በከፊል አርብቶ አደር አካባቢዎች የሚገኙ ወጣቶች ተሳታፊ እንደሚሆኑም አክለዋል፡፡

በተጨማሪም በመንግሥትና መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት የሚሠሩ፣ ተማሪዎች፣ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች፣ ሥራ አጥና አካል ጉዳተኛ ወጣቶች የውይይቱ ተሳታፊ እንደሚሆኑ አቶ አዲሱ አስረድተዋል፡፡

መንግሥት ነሐሴ 13 እና 14 ቀን 2008 ዓ.ም. ከወጣቶች ጋር በሚያካሂደው ውይይት በጠቅላይ ሚኒስትሩና ወጣቶች መካከል ከሚካሄድ የጥያቄና መልስ መርሐ ግብር በተጨማሪ፣ በጎንዮሽ የሚካሄዱ የተለያዩ መድረኮች እንደሚኖሩ አቶ አዲሱ አስታውቀዋል፡፡

- Advertisement -

በዚህም መሠረት ነሐሴ 13 ቀን 2008 ዓ.ም. የኤችአይቪ ሥርጭት ገጽታና የዘርፈ ብዙ ምላሾች አፈጻጸምና ቀጣይ አቅጣጫን የሚመለከት መድረክ በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ እንደሚካሄድ፣ መድረኩን የሚመሩት ደግሞ የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ ዶ/ር ከሰተብርሃን አድማሱ እንደሚሆኑ ተገልጿል፡፡

በተመሳሳይ በዕለቱ በሥራ ፈጠራ ስኬታማ የሆኑ ወጣቶች የከተማ ልማትና ቤቶች ሚኒስትሩ አቶ መኩሪያ ኃይሌ በሚመሩት መድረክ ላይ ተሞክሮአቸውን ለሌሎች ወጣቶች እንደሚያካፍሉ ተገልጿል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ‹‹ኅብረ ብሔራዊ የፌደራላዊ ሥርዓት ግንባታና የወጣቶች ሚና›› የሚል ጽሑፍ ቀርቦ የፓናል ውይይት እንደሚደረግ ይህንን መድረክ የሚመሩት ደግሞ የፌደራልና አርብቶ አደሮች ልማት ጉዳዮች ሚኒስትር አቶ ካሳ ተክለብርሃን እንደሚሆኑ ተገልጿል፡፡

ወጣቶች በችግሮቻቸውና በጉዳዮቻቸው ዙሪያ መፍትሔ የሚያገኙባቸው መድረኮች በተለያዩ ደረጃዎች ሲካሄዱ መቆየታቸውን ያስታወሱት አቶ አዲሱ፣ ተመሳሳይ መድረኮች በአገር አቀፍ ደረጃ ከቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ጋር በ1999፣ በ2000 እና በ2002 ዓ.ም. መካሄዳቸውን አስታውሰዋል፡፡  

ከ2002 ዓ.ም. ጀምሮ ግን የወጣቶች መዋቅር ወደ ሴቶችና ሕፃናት በመሄዱ ምክንያት፣ ከሌሎች ችግሮች ጋር ተዳምሮ መድረኮቹ አለመካሄዳቸውን አቶ አዲሱ አስረድተዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት ግን የወጣቶችና ስፖርት ሚኒስቴር እንደ አዲስ በመደራጀቱና ወጣቶች በጉዳዮቻቸውና በችግሮቻቸው ዙርያ ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊዎችን፣ በተለይም ጠቅላይ ሚኒስትሩን ፊት ለፊት አግኝተው በጉዳዮቻቸው ላይ ለመወያየት ባቀረቡት ጥያቄ መሠረት የሚመካከሩበትን መድረክ መፍጠሩ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ መድረኩ መዘጋጀቱን አቶ አዲሱ ጠቁመዋል፡፡

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

ለከተራና ጥምቀት በዓላት ትኩረት የሚሹት ለኮሪደር ልማት የተቆፋፈሩ መንገዶች

የዘንድሮ የጥምቀት በዓል በተለይ በአዲስ አበባ ለየት ባለ ጥበቃ የሚከበር ስለመሆኑ የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ አስታውቋል፡፡ የደንብ ማስከበር ባለሥልጣንና ሌሎች አካላትም በዓሉ በሰላም...

ኢትዮጵያዊቷ ተማሪ የ2025 የሁዋዌ ዓለም አቀፍ አምባሳደር ሆና ተመረጠች

የሥላሴ ዩኒቨርሲቲ አራተኛ ዓመት የኮምፒዩተር ሳይንስ ተማሪ አሲያ ከሊፋ የሁዋዌ የ2025 የሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር ዓለም አቀፍ አምባሳደሮች አንዷ ሆና ተመረጠች፡፡ ሁዋዌ ከመረጣቸው 12 አምባሳደሮች...

የትግራይ ክልል ተፈናቃዮች የኢትዮጵያ ሕዝብ ወደ ቀዬአችን እንድንመለስ ድምፅ ይሁነን ሲሉ ጠየቁ

ከሰኞ ጥር 5 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ለሦስት ቀናት የተቃውሞ ሠልፍ በመቀሌ ከተማ እያካሄዱ ያሉት የትግራይ ክልል ተፈናቃዮች፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ድምፅ እንዲሆናቸው ጠየቁ፡፡ በፕሪቶሪያ...

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በታጣቂዎችና ሚሊሻዎች መካከል በተከፈተ ተኩስ የሰዎች ሕይወት ማለፉ ተገለጸ

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በመተክል ዞን ቡለን ከተማ፣ በሸኔ ታጣቂዎችና በክልሉ ሚሊሻዎች መካከል በተከፈተ ተኩስ የሰው ሕይወት መጥፋቱ ተሰማ፡፡ የክልሉ ነዋሪዎች ‹‹የሸኔ ኃይሎች›› በማለት ወደ የጠሯቸው...

መንግሥትና ታጣቂዎች በየትኛውም ቦታና ሰዓት ለመነጋገር ዝግጁ ሲሆኑ ለማገዝ ዝግጁ መሆኗን አሜሪካ አስታወቀች

የሲቪክ ምኅዳሩ ሊጠበቅና ሚዲያዎች በነፃነት ሊሠሩ ይገባል ተብሏል ‹‹በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች መንግሥትና ታጣቂዎች ገንቢ በሆነ መንገድ በየትኛውም ቦታና ጊዜ ሰላማዊ ንግግር ለማድረግ ዝግጁ ሲሆኑ ለማገዝ...

መንግሥት ባለፉት አምስት ዓመታት 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ገንብቻለሁ አለ

የንብረት ታክስ አዋጅ እምብዛም ማስተካከያ ሳይደረግበት መፅደቁ ቅሬታ ፈጥሯል መንግሥት ኢሕአዴግ መንግሥት ሆኖ አገሪቷን ሲያስተዳድር ለ14 ዓመታት (ከ1996 እስከ 2010 ዓ.ም.) በአገሪቱ ከገነባቸው ኮንዶሚኒየም የጋራ...

አዳዲስ ጽሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ቀኑን ሙሉ ከዋሉበት የሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ተመልሰው ከባለቤታቸው ጋር እያወጉ ነው]

የምን ስብሰባ ላይ ዋልኩ ነበር ያልከኝ? የሥራ አስፈጻሚ። የምን ሥራ አስፈጻሚ? የገዥው ሥራ አስፈጻሚ። ምን ገጥሟችሁ ነው የተሰበሰባችሁት? ለመረጠን ሕዝብ ቃል የገባናቸውን ተግባራት አፈጻጸም የምንገመግምበት የተለመደ ስብሰባ ነው። የገባችሁት ቃል...

ሕወሓትን አጣብቂኝ ውስጥ የከተተው መመርያ

በሁለት አንጃ ተከፍሎ የእርስ በርስ የቃላት ጦርነት ውስጥ የገባው ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ልዩነቱን ትቶ ወደቀድሞው አንድነቱ በመመለስ የሚጠበቅበትን ጠቅላላ ጉባዔ የማድረግ አልያም...

ባንኮች እየፈጸሙት ያለው አቅርቦትንና ፍላጎትን ያላገናዘበ የውጭ ምንዛሪ ግዥ

የውጭ ምንዛሪ ግብይት በገበያ ዋጋ እንዲገበይ የወጣው ሕግ ተግባራዊ መሆን ከጀመረ ከሰባት ወራት በላይ አስቆጥሯል፡፡ ሕጉ ተግባራዊ በተደረገበት የመጀመርያው ቀን የአንድ ዶላር የምንዛሪ ዋጋ...

አሳረኛው ኑሮ!

የዛሬው ጉዞ ከቦሌ ወደ ፒያሳ ይሆን ዘንድ ግድ ሆኗል፡፡ ለምን? በኑሮ  ምክንያት፡፡ የታክሲ መሠለፊያው ወሬ የነዳጅ ጭማሪውን ተከትሎ ስለሚመጣው ተጨማሪ ታሪፍ ነው፡፡ ‹‹የእኛ ኑሮ...

የግለሰቦች ለመብታቸው ኃላፊነት አለመውሰድ ለአገር ያለው አደጋ

በያሬድ ኃይለመስቀል አንድ የማከብረው ኢኮኖሚስት አንድ መጽሐፍ እንዳነብ መራኝና ማንበብ ጀመርኩኝ። ይህንን መጽሐፍ ሳነበው ከዋናው ሐሳብ ወጣ ብሎ ስለ “የነፃ ተጓዦች ሀተታ” (The Free Rider...

‹‹የብድርና ቁጠባ ኅብረት ሥራ ማኅበራትን ኢኮኖሚያዊ አስተዋጽኦ ማጠናከር ያስፈልጋል›› አቶ ፍፁም አብርሃ፣ የአሚጎስ ብድርና ቁጠባ ኅብረት ሥራ ማኅበር መሥራችና ሥራ አስኪያጅ

አሚጎስ የብድርና ቁጠባ ኅብረት ሥራ ማኅበር ከተመሠረተ አሥራ ሁለት ዓመታት ሆኖታል፡፡ በእነዚህ ዓመታት 8,500 አባላትን ማፍራት ችሏል፡፡ አሚጎስ ስለተመሠረተበት ዓላማ፣ እያከናወናቸው ስለሚገኙ ተግባራት፣ የብድርና...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን