Monday, May 29, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊኦፔራ አቀንቃኟ ታዳጊ ሃና ከአሜሪካ ኤምባሲ ቪዛዋን ተቀበለች

ኦፔራ አቀንቃኟ ታዳጊ ሃና ከአሜሪካ ኤምባሲ ቪዛዋን ተቀበለች

ቀን:

የኦፔራ ሙዚቃ በማቀንቀን የታወቀችው ታዳጊዋ ሃና ግርማ፣ የበርክሌይ ዩኒቨርሲቲ ሙዚቃ ትምህርት ቤት የሰጣትን የነፃ ትምህርት ዕድል ለመጠቀም ከአሜሪካ ኤምባሲ ቪዛ ጠይቃ በክፍሉ ሠራተኛ ብትከለከልም፣ ከአሳዳጊ ሞግዚቷ አርቲስት ቴዎድሮስ መኮንን (ቴዲማክ) ጋር ኤምባሲው ከተነጋገረ በኋላ ቪዛ ሊሰጣት መቻሉ ታወቀ፡፡

ኤምባሲው ለታዳጊዋ ቪዛ የከለከለበትን መንገድ በመጥቀስ ቴዲማክ ያሰማውን አቤቱታ በረቡዕ፣ የሐምሌ 27 ቀን 2008 ዓ.ም ዕትማችን መዘገባችን ይታወሳል፡፡ ቴዲማክ ለሪፖርተር ገልጾ እንደነበረው ‹‹የኤምባሲው ቪዛ ክፍል ባልደረባ የሆነ አሜሪካዊ ሥነ ምግባር በጎደለው ሁኔታ ታዳጊዋን ድምፃዊ አጉላልቷል፣ ሞራሏን በሚነካ መንገድ አስተናግዷታል፡፡››

ዘገባው ከወጣ በኋላ በማግሥቱ የኤምባሲው ቆንስላ ክፍል ኃላፊዎችና የባህል ማዕከል ተጠሪዎች ቴዲማክን ጠርተው በማነጋገርና ያጋጠመውን ጉዳይ እንዲያስረዳ በማድረግ፣ ከዋሽንግተን በተገኘው ይሁንታ አማካይነት ቪዛው ለታዳጊዋ መሰጠቱን ቴዲማክ አስታውቋል፡፡ በዚህም መደሰቱን፣ ‹‹በኤምባሲው ኃላፊዎች ቅሬታዬንና የደረሰብኝን አዳምጠው፣ ያጋጠመኝኝ አላስፈላጊ መጉላላት በመገንዘብ ላደረጉት ትብብር አመሰግናለሁ፤›› በማለት ገልጿል፡፡ የተሰጣቸው ሕጋዊ ኃላፊነት ያለአግባብ በመጠቀም ያለበቂ ምክንያት በርካቶችን ቪዛ የሚከለክሉ የኤምባሲው ባልደረቦችን የኮነነው ቴዲማክ፣ ቅሬታ የሚሰማና ጠርቶ የሚያናግር አምባሳደር፣ ቆንስላ ወይም የሚመለከተው ኃላፊ መኖሩ ጥሩ እንደሆነም ተናግሯል፡፡  

ታዳጊዋ የኦፔራ ሙዚቃ አቀንቃኝ ካለፉት አምስት ዓመታት ወዲህ በኢትዮጵያ የኦፔራ ሙዚቃን በማቀንቀን ትልቅ ዕውቅና ያገኘችው ታዳጊዋ ሃና ግርማ፣ በዓለም መድረክም ተቀባይነት እያገኘች የመጣች ሲሆን፣ ከሰሞኑ ታዋቂው የበርክሌ ዩኒቨርሲቲ የሰጣትን የሥልጠና ዕድል ግን እንዳለፈበት ለማወቅ ተችሏል፡፡ ይሁን እንጂ ከአንድ ዓመት በላይ የሚቆይ ቪዛ ኤምባሲው ስለሰጣት፣ በአሜሪካ ተዘዋውራና ጎብኝታ እንድትመለስ ለማድረግ ማሰቡን ሞግዚቷ ቴዲማክ ጠቅሷል፡፡

ታዳጊ ሃና በኢትዮጵያን አይዶል አማካይነት ለዕውቅና የበቃች ሲሆን፣ በወቅቱ የውድድሩ ዳኞች ከነበሩት አንዱ ቴዲማክ የታዳጊዋ ተሰጥኦ ጎልቶ እንዲወጣ ሲያግዛት እንደቆየና በኋላም አሳዳጊዋና ጠባቂ ሞግዚቷ በመሆን ሙዚቃ እየሠሩ እንደሚገኙ ይታወቃል፡፡ 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የመስቀል አደባባይ የመግቢያ ክፍያ ለምን?

ወጣቶች፣ ሕፃናትና አረጋውያን ሳይቀሩ መንፈሳቸውን የሚያድሱበት እንዲሁም ሐሳባቸውን በነፃነት...

በሕገ መንግሥቱ የተዋቀረው ‹‹የብሔር ፖለቲካ›› እና ‹‹ሥርዓቱ›› ያስከተለው መዘዝና መፍትሔው

(ክፍል አራት) በዓቢዩ ብርሌ (ጌራ) ባለፈው ጽሑፌ (በክፍል ሦስት) አሁን ያለው...

የኢትዮጵያ ኅብረተሰብና የመንግሥት መሪ ምሥል

በበቀለ ሹሜ በ2015 ዓ.ም. መጋቢት ወር ውስጥ ይመስለኛል በ‹ሸገር ካፌ›...

ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ ያደረገው አዋጅ የፍትሐዊነት ጥያቄ አስነሳ

በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ስምንት ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ በማድረግ ተቋማዊና...