- Advertisement -

በአዲስ አበባ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው 400 ሺሕ ሰዎች በምግብ ዋስትና ሊታቀፉ ነው

በአዲስ አበባ ከተማ ከድህነት ወለል በታች የሚገኙ ከ400 ሺሕ በላይ ሕዝቦች  በሴፍቲኔት ፕሮግራም ሊታቀፉ ነው፡፡ ይህ ፕሮግራም ከሚቀጥለው 2009 ዓ.ም. ጀምሮ ለአምስት ዓመታት ተግባራዊ እንደሚደረግ ተገልጿል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ሠራተኞችና ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ አቶ ኤፍሬም ግዛው ዓርብ ሐምሌ 29 ቀን 2008 ዓ.ም. በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ በዚህ ፕሮግራም ያለረዳት የቀሩ ከ66 ሺሕ በላይ አቅመ ደካሞች ይሳተፋሉ፡፡

በዚህ ፕሮግራም የደሃ ደሃ የተባሉ አካል ጉዳተኞች፣ አቅመ ደካሞችና ሴተኛ አዳሪዎች ሲሆኑ በትክክል ችግር ያለባቸው መሆናቸውን የሚቋቋመው የከተሞች የሥራ ዕድል ፈጠራና የምግብ ዋስትና ምክር ቤት አጣርቶ፣ በመጀመርያው ዙር በስድስት ከተሞች በሚጀመረው የሴፍቲኔት ፕሮግራም በአጠቃይ ከ600 ሺሕ በላይ ወገኖች ይሳተፋሉ፡፡ ለዚህም 450 ሚሊዮን ዶላር በጀት ተይዟል፡፡

ከዚህ በጀት ውስጥ 300 ሚሊዮን ዶላር ከዓለም ባንክ የተገኘ ሲሆን፣ ቀሪው በኢትዮጵያ መንግሥት ይሸፈናል ተብሏል፡፡

የከተማ ቤትና ቤቶች ሚኒስቴር ባወጣው መረጃ በሁለም የአገሪቱ ከተሞች የሚገኙ የምግብ ዋስትና ችግር ያለባቸው የደሃ ደሃ የሆኑ የኅብረተሰብ ክፍሎች ለአብነት ጎዳና ተዳዳሪዎች፣ ለምኖ አዳሪዎች፣ ሴተኛ አዳሪዎች ‹‹ሥራ ፈት ዜጎች›› አካል  ጉዳተኞች የአደንዛዥ ዕፅ ተጎጂዎች፣ የአዕምሮ ጤና ሕመምተኞችና ወጣት ጥፋተኛ ተጠቃሾች ናቸው፡፡

መረጃው እንዳለው በዚህ ፕሮግራም 4.7 ሚሊዮን የሚሆኑ ዜጎችን ተጠቃሚ የሚያደርግ ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 3.5 ሚሊዮን ሰዎች ወደ ተለያዩ የሥራ መስኮች ሊሰማሩ የሚችሉ ናቸው፡፡ 1.3 ያህሉ ደግሞ ወደ ሥራ ሊሰማሩ የማይችሉና በቀጥታ የማኅበራዊ ሴፍቲኔት የሚያስፈልጋቸው ናቸው ተብሏል፡፡

- Advertisement -

ይህ ፕሮግራም ተግባራዊ የማድረግ ኃላፊነት በቅርብ ለተቋቋመው የከተሞች ምግብ ዋስትናና የሥራ ዕድል ፈጠራ ኤጀንሲ ይሆናል ተብሏል፡፡

በኢትዮጵያ በተለይ በገጠሩ ክፍል ቀደም ብሎ የምግብ ዋስትና ፕሮግራም ተጀምሮ ብዙ ለውጥ ማምጣቱ ተገልጿል፡፡ ነገር ግን በከተሞች ይህ የምግብ ዋስትና ፕሮግራም ባለመጀመሩ በ2004 ዓ.ም. በተጠና ጥናት 25.7 በመቶ የሚሆኑ የከተማ ነዋሪዎች ለምግብ ዕጦት ተጋላጭ እንደሆኑ ይገልጻሉ፡፡

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

የጤናው ዘርፍ ባለፉት ስድሥት ወራት

የወባ በሽታ ከሰሃራ በታች በሚገኙ የአፍሪካ አገሮች ዋነኛ የጤናና የማኅበራዊ ቀውስ መንስዔ ነው፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት እ.ኤ.አ. በ2024 ያወጣው መረጃም 263 ሚሊዮን ሰዎች የወባ...

በተያዘው ወር መጨረሻ  አዲስ ፖስፖርትና ቪዛ  ይፋ ይደረጋል ተባለ

በውጭ አገር የሚታተመውን ፓስፖርትና አገሪቱ ለውጭ ዜጎች የምትሰጠውን ቪዛ በአዲስ ይዘትና ኅትመት በአገር ውስጥ ታትሞ በተያዘው ወር የካቲት 2017 ዓ.ም. ይፋ እንደሚደረግ የኢሚግሬሽንና ዜግነት...

በውጭ አገር ለሚሰጥ ሕክምና የአገር ውስጥ ተወካይ ኃላፊነት እንዲወስድ የሚያስገድድ ረቂቅ መመርያ ተዘጋጀ

የጤና ሚኒስቴርን ፈቃድ አግኝተው በውጭ አገሮች የሕክምና አገልግሎት ተቋማት የሚታከሙ ኢትዮጵያውያን፣ የሕክምና አገልግሎት ጥራት ደረጃ ጉድለት፣ የሕክምና ስህተት ወይም የሙያ ግድፈት ቢፈጸምባቸው፣ የውጭ ሕክምና...

በአማራ ክልል የአሽከርካሪዎች ዕገታን መደበኛ የሥራ ቦታ አድርጎ የሚንቀሳቀሰው መበራከቱ ተገለጸ

በአማራ ክልል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣው የአሽከርካሪዎች ዕገታ በአሁኑ ወቅት ክፍት የሥራ ቦታ እየሆነ መምጣቱ ተነገረ፡፡ አሽከርካሪዎችን በማገት ከፍተኛ ገንዘብ የሚጠይቁና ሲያዙም በአግባቡ በሕግ...

የባሕር ዳርና ድሬዳዋ ኤርፖርቶች የሲቪል በረራዎች ቁጥጥር ስርዓታቸውን አሳደጉ

በኢትዮጵያ ከሚገኙት አራት ዓለም አቀፍ ኤርፖርቶች መካከል የሆኑት የባህር ዳርና የድሬዳዋ ኤርፖርቶች፣ የአየር በረራዎች ቁጥጥር ክፍሎች ከጥር ወር 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ማናቸውንም እስከ 25...

ኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቱን በርካሽ ዋጋ ማቅረቡ ከተወዳዳሪው ኩባንያ ቅሬታ እየቀረበበት መሆኑን አስታወቀ

ኢትዮጵያ ቴሌኮም ጉልህ የገበያ ድርሻ እያለው አገልግሎቱን በርካሽ ዋጋ ማቅረቡ ለተወዳዳሪው ኩባንያው ውድድሩን አስቸጋሪ ስላደረገበት፣ ‹‹መንግሥታዊ ኩባንያው ዋጋ እንዲጨምር መገደድ አለበት የሚል የቅሬታ ጥያቁ...

አዳዲስ ጽሁፎች

የጤናው ዘርፍ ባለፉት ስድሥት ወራት

የወባ በሽታ ከሰሃራ በታች በሚገኙ የአፍሪካ አገሮች ዋነኛ የጤናና የማኅበራዊ ቀውስ መንስዔ ነው፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት እ.ኤ.አ. በ2024 ያወጣው መረጃም 263 ሚሊዮን ሰዎች የወባ...

የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት በባለሙያ ዓይን

(በጎ ጎኖችና እርምት የሚፈልጉ ጉዳዮች) በዮሐንስ መኮንን በጥር ወር 2016 ዓ.ም. የአዲስ አበባ ዋና ዋና ኮሪደሮችን በማዘመን ከተማዋን ለነዋሪዎቿና ለጎብኚዎቿ ምቹ ያደርጋታል የተባለ ፕሮጀክት በ43 ቢሊዮን...

በልዩነት ውስጥ ሆነንም እስኪ እንነጋገር

በገነት ዓለሙ ዴሞክራሲ መብቶችና ነፃነቶች የሚሠሩበት የሕዝብ አስተዳደር ነው፡፡ ሰብዓዊ መብቶችንና ነፃነቶችን መኗኗሪ ያደረገ ሥርዓት ነው፡፡ እነዚህ መሠረታዊ መብቶችና ነፃነቶች በተፈጥሮ የተገኙ፣ ሰው በመሆናችን ብቻ...

ለጤናማ የትራፊክ ፍሰትና ለመንገድ ደኅንነት ቅጣት መጣል ብቻውን መፍትሔ አይሆንም!

በአዲስ አበባ ከተማ ለተሽከርካሪዎች ምቹ የሆኑ መንገዶችን እየተመለከትን ነው፡፡ ከአዳዲሶቹ መንገዶች ባሻገር አንዳንድ ነባር መንገዶች የማስፋፊያ ሥራ ታክሎባቸው አገልግሎት ላይ ውለዋል፡፡ ከኮሪደር ልማቱ ጋር...

የግጭት አዙሪት ውስጥ ሆኖ የአፍሪካ ማዕከል መሆን ያዳግታል!

የአፍሪካ ኅብረት 38ኛው የመሪዎች ጉባዔ በአዲስ አበባ ሲካሄድ ብዙ ትዝ የሚሉ ጉዳዮች አሉ፡፡ እጅግ በጣም አሰልቺ፣ ውጣ ውረድ የበዛበትና ታላቅ ተጋድሎ ተደርጎበት ከከፍተኛ ዲፕሎማሲያዊ...

አገሬ ምንተባልሽ – ልብ ያለው ልብ ይበል

በቶማስ በቀለ ይቺ አገራችን ብዙ ተብሎላታልም፣ ብዙ ተወርቶባታልም፣ አገሪቱ በቅኝ ያልተገዛች ብቸኛ አገር (ላይቤሪያን ጨምሮ) ከመሆኗ አኳያ የሚነገርላት ብዙ ጥሩና የሚገርሙ ነገሮች ያሉትን ያህል፣ ከረሃብ...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን