Monday, October 2, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናአገር በመክዳትና በሽብር ወንጀል ውስጥ ተሳትፈዋል የተባሉ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ተከሰሱ

አገር በመክዳትና በሽብር ወንጀል ውስጥ ተሳትፈዋል የተባሉ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ተከሰሱ

ቀን:

ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ለመጠበቅ የተጣለባቸውን አደራ በመተው፣ የኦነግን የሽብር ተልዕኮ ለመፈጸም አባል ሆነውና ሌሎችንም ሲመለምሉ ነበር የተባሉ አምስት የመከላከያ ሠራዊት ባልደረቦች፣ የሽብር ተግባር ወንጀል በመፈጸም ተጠርጥረው ክስ ተመሠረተባቸው፡፡

ተከሳሾቹ የደቡብ ምዕራብ ዕዝ አባላት መሆናቸውንና በሶማሌ ክልል ልዩ ስሙ ካሉብ ነዳጅ ማውጫ አካባቢ ተመድበው ይሠሩ እንደነበር፣ የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ የመሠረተባቸው ክስ ያስረዳል፡፡

በሽብር ተግባር ወንጀል የተከሰሱት ወታደር ኢብራሂም ጉሬ፣ ምክትል አሥር አለቃ እስክንድር አደም፣ አሥር አለቃ ሽመልስ ብርሃኑ፣ ወታደር ጫላ ኢሳና ወታደር ሀብታሙ ፋና መሆናቸውን፣ ሁሉም ተከሳሾች የሱማሌ ክልል ቆራኔ ደብወይኒ ነዋሪዎች መሆናቸው በክሱ ተጠቁሟል፡፡

ተከሳሾቹ ተመድበው ይሠሩበት የነበረውን ወታደራዊ ተግባር በአግባቡ መፈጸም ሲገባቸው፣ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ዓላማ ለማስፈጸም፣ የሠራዊቱን አባላትና ሌሎችን በአባልነት ይመለምሉ እንደነበር ዓቃቤ ሕግ በክሱ አስረድቷል፡፡ በሶማሌ ክልል ልዩ ስሙ ካሉብ ነዳጅ ማውጫ ተብሎ በሚጠራው ሥፍራ፣ በግዳጅ ላይ የነበሩ የጦር ሠራዊት አባላትን ይመለምሉ እንደነበርም ተገልጿል፡፡

‹‹ኦነግን እንቀላቀል›› በማለት የታጠቁትን የጦር መሣሪያ እንደያዙ በቅስቀሳና ምልመላ ላይ መሳተፋቸውን ዓቃቤ ሕግ በክሱ ገልጿል፡፡ ተከሳሾቹ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 32(1ሀ)፣ 38 እና የፀረ ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀጽ 7(1) ሥር የተደነገገውን ተላልፈው መገኘታቸው፣ በፈጸሙት የሽብርተኛ ድርጅት ውስጥ መሳተፍ ወንጀል ክስ ቀርቦባቸዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ተመድንና ዓለም አቀፋዊ ሕግን ከእነ አሜሪካ አድራጊ ፈጣሪነት እናድን!

በገነት ዓለሙ በእኔ የተማሪነት፣ የመጀመርያ ደረጃ ተማሪነት ጊዜ፣ የመዝሙር ትምህርት...

የሰላም ዕጦትና የኢኮኖሚው መንገራገጭ አንድምታ

በንጉሥ ወዳጅነው ፍራንክ ቲስትልዌይት የተባሉ አሜሪካዊ ጸሐፊ ‹‹The Great Experiment...

ድህነት የሀብት ዕጦት ሳይሆን ያለውን በአግባቡ ለመጠቀም አለመቻል ነው

በአንድነት ኃይሉ ድህነት ላይ አልተግባባንም፡፡ ብንግባባ ኖሮ ትናንትም ምክንያት ዛሬም...