Wednesday, October 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናበሺዎች የሚቆጠሩ ደጋፊዎቻቸው ለዶ/ር መረራ ጉዲና አቀባበል አደረጉ

በሺዎች የሚቆጠሩ ደጋፊዎቻቸው ለዶ/ር መረራ ጉዲና አቀባበል አደረጉ

ቀን:

ዛሬ ጥር 9 ቀን 2010 ዓ.ም. ቀትር በኃላ ለዶ/ር መረራ ጉዲና ከእስር ቤት መለቀቃቸውን ተከትሎ በሺሕዎች የሚቆጠሩ ደጋፊዎቻቸው በዶክተሩ መኖሪያ አካባቢ ተገኝተው አቀባበል አደረጉላቸው። የተጠረጠሩበት ክስ በመንግሥት ተቋርጦ ከእስር ቤት የተለቀቁት / መረራ፣አዲስ አበባ ወደ አምቦ በሚወስደው ዋና መንገድ አሸዋ ሜዳ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ወደሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ከቀትር በኃላ ገብተዋል፡፡ለዶክተር መረራ ከበርካታ ኪሎ ሜትሮች ጀምሮ እስከ መኖሪያ ቤታቸው ድረስ በሺሕዎች የሚቆጠሩ ደጋፊዎቻቸው ጎዳና ወጥተው የሞቀ አባበል አድርገውላቸዋል።

መኖሪያ አካባቢያቸው ተገኝተው አቀባበል ላደረጉላቸው ደጋፊዎቻቸውም / መረራ በኦሮሚኛ ቋንቋ ንግግር አድርገዋል። ወደ መኖሪያ ቤታቸው ከገቡ በኃላም ለአገር ውስጥና ለውጭ ጋዜጠኞች አጭር መግለጫ አድርገዋል።

በዚህ መግለጫቸውም ከእስር መለቀቃቸውን ያደነቁ ሲሆን፣ በቀጣይ ስለሚያደርጉት የፖለቲካ ትግል ከፓርቲያቸው ጋር በመመካከር እንደሚያሳውቁ ገልጸዋል። ሌሎች ፖለቲከኞችም ይፈታሉ የሚል እምነታቸውንም ተናግረዋል።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

[ክቡር ሚኒስትሩ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው በቴሌቪዥን የሚተላለፈውን ዜና በመገረም እየተመለከቱ አገኟቸው]

ምንድነው እንዲህ ቀልብሽን የሳበው? ስለሰላም ኖቤል ሽልማት ዜና እየተመለከትኩ ነበር። እና...

የወሎ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ መመሥረትና የአማራ ክልል ጥያቄ

አማራ የኢሕአዴግ አንዱ መሥራችና አጋር ከሆነው ብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ...

የሽንኩርት ዋጋ ሰማይ የነካበት ምክንያት ምንድነው?

ባለፉት ሁለትና ሦስት ሳምንታት የሸማቾችን ኪስ ካስደነገጡ መሠረታዊ ከሚባሉ...

የአዲስ አበባ ንግድ ምክር ቤት ኤግዚቢሽን ማዕከልን እንዲያስተዳድር የተሰጠው ኮንትራት ለምን ተቋረጠ?

በአዲስ አበባ ከተማ ለንግድ ትርዒት ዝግጅት ብቸኛ በመሆን የሚጠቀሰው...