Wednesday, October 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናበወልዲያ ከተማ በተከሰተ ግጭት የበርካታ ሰዎች ሕይወት አለፈ

በወልዲያ ከተማ በተከሰተ ግጭት የበርካታ ሰዎች ሕይወት አለፈ

ቀን:

ትናንት ጥር 12 ቀን 2010 ዓ.ም. የቃና ዘገሊላ በዓልን ለማክበር በወጡ ወጣቶችና በፀጥታ ኃይሎች መካከል በተፈጠረ ግጭት የበርካታ ሰዎች ሕይወት ማለፉ ታወቀ፡፡ የአማራ ክልል የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ንጉሱ ጥላሁን በፌስቡክ ገጻቸው ላይ እንዳስታወቁት፣ የሞቱት ሰዎች ቁጥርና ምክንያቱ ምን እንደነበር ገና ይጣራል፡፡

የሪፖርተር ምንጮች ከስፍራው እንዳስታወቁት፣ በዓሉን ለማክበር የወጡ ወጣቶች ፖለቲካዊ መልዕክት ያላቸውን ዘፈኖች ሲዘፍኑ እንደነበርና በፀጥታ ኃይሎች እንዲያቆሙ ቢነገራቸውም ለማቆም ፈቃደኛ ሳይሆኑ በመቅረታቸው ግጭቱ ተቀስቅሷል፡፡

ግጭቱ ትናንትና የጀመረ ቢሆንም፣ በከተማው ግን እስካሁን ድረስ የሚሰማ የተኩስ ድምጽ እንዳለ የሪፖርተር ምንጮች ከስፍራው ገልጸዋል፡፡

የማኅበራዊ ሚዲያው ተጠቃሚ የሆኑ የተለያዩ የኅብረተሰብ አካላትም በግጭቱ ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖች ሐዘናቸውን እየገለጹ ይገኛሉ፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

[ክቡር ሚኒስትሩ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው በቴሌቪዥን የሚተላለፈውን ዜና በመገረም እየተመለከቱ አገኟቸው]

ምንድነው እንዲህ ቀልብሽን የሳበው? ስለሰላም ኖቤል ሽልማት ዜና እየተመለከትኩ ነበር። እና...

የወሎ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ መመሥረትና የአማራ ክልል ጥያቄ

አማራ የኢሕአዴግ አንዱ መሥራችና አጋር ከሆነው ብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ...

የሽንኩርት ዋጋ ሰማይ የነካበት ምክንያት ምንድነው?

ባለፉት ሁለትና ሦስት ሳምንታት የሸማቾችን ኪስ ካስደነገጡ መሠረታዊ ከሚባሉ...

የአዲስ አበባ ንግድ ምክር ቤት ኤግዚቢሽን ማዕከልን እንዲያስተዳድር የተሰጠው ኮንትራት ለምን ተቋረጠ?

በአዲስ አበባ ከተማ ለንግድ ትርዒት ዝግጅት ብቸኛ በመሆን የሚጠቀሰው...