Thursday, June 1, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናበወልዲያ በተከሰተው ግጭት የሞቱት ሰዎች ቁጥር ሰባት ደረሰ

በወልዲያ በተከሰተው ግጭት የሞቱት ሰዎች ቁጥር ሰባት ደረሰ

ቀን:

በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ወልዲያ ከተማ ትናንት ጥር 12 ቀን 2010 ዓ.ም. እና ዛሬ ጥር 13 ቀን 2010 ዓ.ም. በፀጥታ ኃይሎችና የቃና ዘገሊላ በዓልን ለማክበር በወጡ ሰዎች መካከል በተከሰተው ግጭት እስካሁን የሰባት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ ኃላፊ ኮማንደር አማረ ጎሹ ለአማራ ቴሌቪዥን በሰጡት የስልክ ማብራሪያ ገለጹ፡፡

 

አንድ የፀጥታ ኃይል አባልና ሌሎች ስድስት ሰዎች ሞተዋል ያሉት ኮማንደሩ፣ ሁለት የፖሊስ አባላት ከፍተኛ የአካል ጉዳት እንደደረሰባቸው ገልጸዋል፡፡ በአጠቃላይ የአካል ጉዳት የደረሰባቸው 15 ሰዎች መሆናቸውንም ኮማንደሩ አስታውቀዋል፡፡

 

ኮማንደሩ አክለውም ዛሬ ከጠዋቱ አንድ ሰዓት ጀምሮ በነበረ ግጭት መኪኖች፣ ቤቶችና ሆቴሎች መቃጠላቸውን ተናግረዋል፡፡

የክልሉ የፀጥታ ኃይል ግጭቱ እዚህ ደረጃ ሳይደርስ ለማስቆም ጥረት ሲደረግ የነበረ ቢሆንም፣ የተወሰኑ የበዓሉ ተሳታፊዎች የፖሊስ አባላትን አሳደው በድንጋይ ለመደብደብ ባደረጉት ሙከራ ይህን ያክል ጉዳት ሊደርስ ችሏል ብለዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...