Sunday, September 24, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናበኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን የሚገኘው የታንታለም ማምረቻ መዘጋቱ ውዝግብ ፈጠረ

በኦሮሚያ ክልል ጉጂ ዞን የሚገኘው የታንታለም ማምረቻ መዘጋቱ ውዝግብ ፈጠረ

ቀን:

የኦሮሚያ ክልል በጉጂ ዞን የሚገኘውንና የፌዴራል መንግሥት ተቋም የሆነውን የቂንጢቻ ታንታለም ማዕድን ማምረቻ መዝጋቱ በክልሉና በፌዴራል መንግሥት መካከል ውዝግብ ፈጠረ፡፡

የማዕድን ማምረቻው እንዲዘጋ የተወሰነው በአካባቢውና በማኅበረሰቡ ላይ ጉዳት እያደረሰ ነው በሚል ምክንያት ቢሆንም፣ ዋና ምክንያቱ ግን የማዕድን ይዞታውን ለአካባቢው ወጣቶች ተሰጥቷቸው ራሳቸው አምርተው በመሸጥ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ታስቦ መሆኑን ከሁለቱም ወገኖች ሪፖርተር ያሰባሰባቸው መረጃዎች ያመለክታሉ።

የማዕድን፣ ነዳጅና ባዮፊዩል ኮርፖሬሽን ላለፋት 28 ዓመታት ማዕድኑን በማምረት ለውጭ ገበያ ሲቀርብ የነበረ ሲሆን፣ ማዕድኑን እዚሁ በማቀነባበርና እሴትመጨመር ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ እንዲያስገኝ የፌዴራል መንግሥት መወሰኑ ይታወቃል። በውሳኔው መሠረትም ኮርፖሬሽኑን የሚቆጣጠረው የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ሚኒስቴር የቂንጢቻ ታንታለም ማምረቻን በከፊል ለመሸጥ ዓለም አቀፍ ጨረታ አውጥቶ ነበር፡፡ ሆኖም በክልሉና በኮርፖሬሽኑ መካከል የተፈጠረው ውዝግብ ይህ ጨረታ በወጣበት ወቅት ነው፡፡

ኮርፖሬሽኑ ለአካባቢው ወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር በየዓመቱ ሦስት ሚሊዮን ብር በጀት እንደሚመድብ ያቀረበውአማራጭ ሐሳብም በዞኑ አስተዳደር ተቀባይነት አላገኘም። ይህንን አጣብቂኝ ሁኔታ ለመፍታትና የቂንጢቻ ታንታለም ማዕድን ማምረቻን ለውጭ አልሚዎች በከፊል ለማዘዋወር የወጣው ጨረታና የተጀመረው ጥረት እንዳይስተጓጎል ለማድረግ የኮርፖሬሽኑ ተቆጣጣሪ የሆነው የመንግሥት ልማት ድርጅቶች ሚኒስትር አቶ ግርማ አመንቴ የሚመራ ኮሚቴ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ ለማ መገርሳን ለማነጋገር መወሰኑን ያገኘናቸው መረጃዎች አመልክተዋል።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የቤት ባለንብረቶች የሚከፍሉትን ዓመታዊ የንብረት ታክስ የሚተምን ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ

በአዋጁ መሥፈርት መሠረት የክልልና የከተማ አስተዳደሮች የንብረት ታክስ መጠን...

እንደ ንብረት ታክስ ያሉ ወጪን የሚያስከትሉ አዋጆች ከማኅበረሰብ ጋር ምክክርን ይሻሉ!

የመንግሥትን ገቢ በማሳደግ ረገድ አስተዋጽኦ እንዳላቸው የሚታመኑት የተጨማሪ እሴት...

ለዓለምም ለኢትዮጵያም ሰላም እንታገል

በበቀለ ሹሜ ያለፉት ሁለት የዓለም ጦርነቶች በአያሌው የኃያል ነን ባይ...