Wednesday, March 22, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
እኔ የምለዉየኢሕአዴግ ዕጣ ፈንታ በድርጅታዊ ፊዚክስ ዓይን

የኢሕአዴግ ዕጣ ፈንታ በድርጅታዊ ፊዚክስ ዓይን

ቀን:

ጌታቸው አሰፋ (ዶ/ር)

አንድ የሆነ ነገር እንዴት ነው የሚራው?’ ብሎ መሠረታዊ መርሆች ላይ ለመድረ መጣር ዘመን አመጣሽ አዲስ ፍላጎት ሳይሆን የሰው ልጆች በዚህ ምድር መኖር ከጀመሩበት ጊዜ ጀምሮ የነበረ ይመስለኛል ሰዎች እሳትን ለመጀመሪያ ጊዜ ካዩበት ቅጽበት ምናልባትም እንዴት ነው የሚራው ብለው ከመጠየቃቸው በፊት አስቀድሞ ሌሎች ነገሮችን ራር እንዴትነት ሲጠይቁ ነበር። አዳምና ሔዋን ዕፀ በለስ ሲበሉ ምናልባትም ሰይጣን የነገራቸው ነገር ‘እንዴት ነው የሚራው?’ የሚለው ጥያቄ በሳባቸው ውስጥ ከነበረስ ማን ያውቃል? ሳይንሳዊ ምርምር ቅርፅ ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ፣ እንዲሁም የሰው ልጆች ዘመናዊ ማተሚያን ጥቅም ላይ ካዋልን በኋላ ነገሮች ራር እንዴትነት ዙሪያ ያለን እውቀት በከፍተኛ ደረጃ ንሯል። ጋራ እውቀታችን ባደገ ቁጥር‹‹የምር ግን እንዴት ነው የሚራውና የሚ(!)ራው?›› እያልን መቀጠላችን ነው አዳዲስ ግኝቶች የሚወልደው

በተለይ ዛሬ ላይ ሆነን እንደ ኢትዮጵያ ዝብ መልስ ብናገኝላቸው ይጠቅሙናል ከማስባቸው ጉዳዮች አንዱአዴግ እንዴት ነው የሚራው?” የሚለው ጥያቄ ነው።እርግጥ ይህን ጥያቄ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በራሱ በኢሕአዴግ በተቃዋሚዎቹና በተራው ሕዝብ በተለያ ጊዜያት ዘርፈ ብዙ መልስ የተሰጠበትና የሚሰጥበት እንደሆነ አላጣሁትም። ነዚህ አካላት በሚሰጠው መልስ  ዙሪያ ከመልሱ ይልቅ ቁምነገሩ ያለው መልስ ለማግኘት የሚጠቀሙበት ዘዴ ነው። ኢሕአዴግ በዚህ ምላሽ ፕሮጋንዳዊ መንገድ ነው የሚከተለው፡፡ ተቃዋሚዎችባላንጣችንእንዴት ነው የሚራው ይነት ትንታኔ ነው የሚሰጡት። ተራው ሕዝብ የተቃዋሚዎችን መልስ መነሻ አድርጎ ዚያ ላይ የተለያዩ የአሻጥር መላምቶችን ጨምሮ ነው የሚያሰፋው። ይኸው በዚህ መንገድ እየተጓዝን ሁለት ርት ዓመታትን አልፈን ወደ ሦስተኛው እየተጠጋን ነው።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ችግሮቻችን ተባብሰው እንደ ገር እንደ ሕዝብ ያለብንን ጫና እጅግ እየከበደ እንደመጣ እገነዘባለሁ። ዜጎች በማንነታቸው ተለይተው የሚጠቁበት ሁኔታ ውስ ገብተናል። ‘አፍሪካ ውስጥ የትም ቦታ እንግዳ አይደለሁም። ልሆንም አልችልም!’ በሚል እሳቤ የፓን አፍሪካ እንቅስቃሴ ሰዎችን ትደግፍ በነበረችው ኢትዮጵያ ውስጥምሳ ዓመታት በኋላ ኢትዮጵያዊያን ኢትዮጵያ ውስጥ እንግዳነት እንሰማቸው ከመሆን አልፈውይወታቸው ለንብረታቸው የሚፈሩበት ብቻ ሳይሆን በማንነታቸው ተለይተው የሚሞቱበት ንብረታቸው የሚቃጠልበት ሁኔታ እየተደጋገመ ነው።  

ኢሕአዴግ በሚያስተዳድራት ኢትዮጵያ እዚህ ደረጃ ላይ ሲደረስ እንደ ድርጅት ከቆየበት የጊዜ ርዝመት ረገድ ከሰደደው አኳያ እንደ ድርጅትመዋቅሬ አደረጃጀቴ ርዕዮተ ዓለሜ ወዘተ እንዴት ነው የሚራው?’ ብሎ ራሱን መፈተሽና ራሱን መረዳት አለበት። እስካሁን እንደነበረው አሁንም በቅርቡ እንደሆነው ከዓመታት በፊት በዚህ ጋዜጣ እንደተባለው ‘ራሱ ንሰሐ ገቢ ራሱ ንሰሐ ተቀባይ ራሱ ይቅርታ ጠያቂ ራሱ ይቅር ባይ’ ሆኖ ከመቀጠል ይልቅ ‘ወዴት እየሄድኩ ነው? አገሪቱስ ወዴት እየወሰድኳት ነው? ዕጣ ፈንታዬስ ምንድነው?’ ብሎ መጠየቅ አለበት ኢሕአዴግ። ይህን ጥያቄ ከምር ጠይቆ ከሱ ው የሆኑ የተለያየ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ መሠረት ያላቸው ኢትዮጵያዊያንን አሰባስቦ ወይም እንዲሰባሰቡ ፈቅዶ አዲስ መልስ ሲያገኝና ወደ ተግባር ሲገባ ብቻ ነው አሁን እንደ ፓርቲ ወደፊት ደግሞ እንደ ተቃዋሚ ፓርቲ መቀጠል የሚቻለው ብዬ አምናለሁ። እንደዚያ ሲሆን ደግሞ ለራሱ ብቻ ሳይሆን ለአገራችንም ጥሩ ይሆናል።

ኢሕአዴግ ያሉበትን በርካታ ችግሮች ለመፍታት ጊዜና ጉልበት መጠየቁ አይቀርም።  ይሁንና መደረግ ያለበት ከተደረገ እንጂ ከላይ እንዳልኩት ራሱ ለራሱ ወይም ለሕዝቡ እስካሁን እንደተለመደው የአፈጻጸም ችግር ነው ያለብኝ’ ብሎ መቀጠሉ የትም አያደርሰውም። በፕሮጋንዳ ሳይሆን የምር የሆነ ጥራትና ቀጣይነት ያለው ሕዝ የሚያምንበት ሳብና አካሄድ ቅደም ተከተል ማበጀት በፍጥነት መተግበር ያስፈልገዋል በይፋም በህቡዕም የሚገጥመውን ተቃውሞ መጠንና ኃይል በጉልበት በመጨፍለቅ ሳይሆን፣ ሕዝቡን የማርካት ርምጃዎች በመውሰድ ማለዘብ ያስፈልገዋል

ለረጅም ጊዜ መቆየቱን መነሻ አድርጎ ይህም ያልፋል ብዙ ነገርም አልፈን መጥተናልማለት ይቅል ለአዳዲስ ዕይታዎች ድም ክፍት የሆኑ ዓይኖችና ጆሮዎች ሊኖሩት ይገባል። አለበለዚያ ምንጣፉ ከእግሩ ሥር እየተጎተተ መሄዱ የግድ መሆኑን ማወቅ አለበት።

‘አንድ ይነት ነገር እየደጋገመ በማድረግ የተለየ ውጤት የሚጠብቅ ሞኝ ነው’ የሚባል ነገር አለ። ከላይ ወደ ታች፣ ከታች ወደ ላይ የሚዘረጉ አስተዳደራዊ መዋቅሮች፣ መረጃ ላይ የተመረቱ አሠራሮችደንበኛ ማዕከል ያደረጉ መንገዶችአርሶ አደር ተኮር ልማታዊ፣ ከኪራይ ሰብሳቢነት የተላቀቀ፣ ወዘተ እያሉ የአንድ ሰሞን ዘመቻዎች የተለመዱ ናቸው እነዚህ ሁሉ ግን እንዳሁኑ የምር ተግዳሮቶች ሲያጋጥሙ እንቅፋቶች ሲበዙ፣ ከፊት ለፊት የተደቀኑ ምርጫዎች ግራ ሲያጋቡ፣ ድርጅቱንም አገሪቱንም መሄድ ወዳለባቸው ትክክለኛ አቅጣጫ ማስኬድ የሚቻለው እንዴት ነው?  ለሚለው ዓቢይ የሚመጥኑ መልሶች አይሆኑም። ያለፈ ልምድ ላይ መተማመን የሚቻለው መቼና የት ነው? ቼስ ነው ፍንትው ያለ ነገር እንዳይታየን የሚያደርገን?በአሁኑ ጊዜ ኢሕአዴግ ማድረግ ያለበት ትክክለኛው ነገር ምንድነው? የድርጅቱ የአሁንና የወደፊትም ውጤታማነት ከፍ ለማድረግ የሚቻለው እንዴት ነው? ‘ድርጅቱ ውስጥ ምን እየሆነ ነው ያለው? በሚሉት ጥያቄዎች ዙሪያ ጥርት ያለ መረዳት መፍጠር ወሳኝ ይመስለኛል።

ድርጅታዊ ዚክ

ጥሩ ሐኪም የሕመም ምልክቶችን በአግባቡ ለመረዳት መጀመሪያ የሰውነታች ብልቶች በአጠቃላይ አንድ ላይ እንዴት እንደሚ ማወቅ ያለበት ይመስለኛል። በተበታተኑ ምልክቶች ብቻ ሳይነዳ አጠቃላይ የሕመሙን ርዓታዊ መነሻ ለማወቅ ቢሞክር ነው ሁነኛ መረዳትና ፍቱን መድኃኒት ለማዘዝ የሚችለው።

ኢሕአዴግም ውስጣዊ ድርጅቱ በተለይ የካድሬ እንዴት እየ እንዳለና እንዴት ራት እንዳለበት የምር ካልተረዳው ለስኬቱም ለውድቀቱም እውነተኛውን መነሻ ማስቀመጥ አይችልም።ዚህ ጋና ነፍስ ሆኖ የቀረበውድርጅታዊ ፊዚክስ’ የንግድ ኩባንያም ሆነ ሌላ ዓይነት ድርጅት የፖለቲካ ፓርቲን ጨምሮ ሙሉ ውስጣዊም ውጫዊ ሥርዓቱን በማየት መፍትሔ ለመፈለግ የሚያግዝ ዓተያይ ነው። የድርጅቱን ሁለንተናዊ ስኬት ለማምጣት፣ በውስጡ ያሉ የተለያዩ ቡድኖች ውጤታማነትን ለማጎልበት፣ የአባላቱን እውነተኛ ዕርካታ ከፍ ለማድረግ የሚረዳ፣ ከተራው አባል እስከ ሙሉ ድርጅቱ የሚፈትሽ ምልከታ ነው ድርጅታዊ ፊዚክስ።

የኢሕአዴግ ተራ አባል እንኳ ላልሆነ ቢጤ ግለሰብ የድርጅቱን አሠራር ማወቅም ሆነ እንዴት ሊሻሻል እንደሚችል መናገር እንዴት ይቻለዋል? መልሱ ወዲህ ነው።  የድርጅታዊ ፊዚክስ አራማጅ የሆነው ሌክስ ሲስኒ  እንደሚለው በተፈጥሮ ፊዚክስ ጠቅላይ መርሆች ላይ ተመርቶ እየተገፋበት ያለውን ድርጅታዊ ፊዚክስን ተጠቅሞ ማንኛውንም ይነት ድርጅት እንደ ድርጅት መፈተሽና መተንተን ይቻላል የሚለው ነው የዚህ ጽሑፍ መነሻም መድረሻም። ዚያ ላይ የኢትዮጵያን ፖለቲካ ይሁነኝ ብለው በቅርብ ርቀት ከሚከታተሉ ሰዎች አንዱ አድርጌ ነው ራሴን የምቆጥረው። ለዓመታት የተጠራቀመው ምልከታ ፍተሻው ውስጥ መንባረቁ አይቀርም።

ደረቁ ፊዚክስ ቁስንና ኃይልን ለየብቻ ዚያ አልፎ በሁለቱም መካከል ያለውን መስተጋብር የሚያጠና መስክ ነው። መስኩ ተፈጥሮ ር መሠረቱ ሲታይ እንዴት እንደሚራና እንደሚናኝ ለመረዳት ይሞክራል። የፊክስ ጎች በኬሚስትሪም በባይሎጂም  ክምናም በምህንድስናም ጥቅም ላይ የሚውሉ በመሆናቸው ፊዚክስ የሳይንሶች ሁሉ መሠረት ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። ደረቁን ፊዚክስ ከተለመደው ምኅዳሩ አውጥተን ይነተ ብዙ ድርጅቶችን ቀረብ ብለን ለማጥናት መጠቀም እንችላለን ነው የድርጅታዊ ፊዚክስ መዘውር። ድርጅታዊ ፊዚክስ ድርጅቶችን በሰላ ዓይን የምናይበትን ሁለንተናዊ መነጽር ይሰጠናል። ድርጅቶችን የምንገልጽበትን ቋንቋ ለትንተና የምንጠቀምባቸው የገፊና ውጤት ክትትሎሽ ጽንሰ ሳቦችን ያቀብለናል። የድርጅቶች የተፈጥሮ ባህርያትቅጣቸውና ጠባዮቻቸውን ለመረዳት የሚያግዙን ነገሮችን ያደርስልናል።

ፊዚክስ የሚያቀብለን ቋንቋ ባህል ተሻጋሪና መልክዓ ምድር ዘለል የሆነ ትርጉም እንዲኖረው አድርጎ ነው። ኢትዮጵያዊው የፊዝክስ ሊቅ ከፈረንሣዊው ወይም ከካናዳዊው በዚህ የዘርፋቸው ቋንቋ ያለምንም ችግር ይግባባ ፊዚክስ  የገፊና ውጤት ተከታትሎ መምጣት እሳቤ አንድ የሆነ ነገር ሲደረግ አስቀድሞ የሚታወቅ ቦታ ጊዜ የማይገደብ ውጤት እንደሚገኝ ያስረዳናል። ኤሌክትሪካዊም ሆኑ ሥነ ሕይወታዊና መሰል ሥርዓቶች የሚጋሯቸው ቅጦች፣ ጠባዮችና ባህርያት አሏቸው፡፡ በአማናዊው ፊዚክስ ጎች መሠረት።  በሌላ አባባል ነባሮቹ የፊዚክስ ሕጎች ዘዋሪ ሚና ከእንጀራ መጋገሪያ ምጣዳችን አንስቶ በጠፈር መንኮራኩር በኩል የተፈጥሮ ነ ምኅዳርን አካቶ እስከ ከዋክብት ርዓትና ከዚያ በላይ ይሄዳል። እነዚህ ጎች እንደ ግለሰቦች፣ ቤተሰቦች ኩባንያዎች ገሮች መሰል ‘ውስብስብና ተለዋዋጭ ሥርዓቶች’ ላይ ተግባራዊ ሚና አላቸው። በአንድ ቃል እነዚህ ውስብስብ፣ ተለዋዋጭ ወይም ተስማምቶ አዳሪ ሥርዓቶች “ድርጅቶች” ብለን እንግለጻቸው። 

ድርጅታዊ ፊዚክስ የድርጅቶች ክንዋኔ መነሻና መድረሻ ነፀብራቅ የሆኑ መሠረታዊ ሥርዓቶችን ያሳውቀናል። ክንዋኔውን ለማሻሻል መደረግ ያለበትን ነገር ለመለየት የሚያስችል የጋራ መነጽር፣ የጋራ ቋንቋ፣ ብሎም የገፊና ውጤት ቅደም ተከተልን ያስለየናል

እንደ ሌክስ ሲስኒ አባባል የድርጅታዊው ፊዚክስ መሠረታዊ ሐሳብ ከላይ የተጠቀሰውን በድርጅቶች ውስጥ የተሻለ ክንዋኔ ማሳካት ነው። ዚህ አቅጣጫ መጓዝ ለድርጅቶች ውጤታማ መሆን ወሳኝ ነው ፊዚክስ የቁስ አካል የኃይል ብሎም የሁለቱ መስተጋብር ሳይንስ ነው ካልንየአስተዳደር ሳይንስ” ደግሞ ድርጅቶችን ለመምራት ጥቅም ላይ ሊውሉ የሚችሉ መርሆችንና ዘዴዎችን የሚያመለክት ከሆነ ድርጅታዊው ፊዚክስ” ደግሞ ሁለቱን አስተሳስሪ አድርገን መቁጠር እንችላለን።

በአገራችን ኅብረተሰቡ በተለይ ወሳኝ ክፍል የሆነው ወጣቱ የቴክኖሎጂ አጠቃቀሙ በከፍተኛ ደረጃ በተለወጠበት ዘመን ሳይቀር፣ የኢሕአዴግ አብዛኛዎቹ የአስተዳደር ንድፈ ሳቦ ለዘመናችን የማይመጥኑ የወጣቱንም ሆነ የሌላውን ኅብረተሰብ ወቅታዊ ፍላጎት ግምት ውስጥ ያላስገቡ ድሮ ላይ የተቸከሉ ናቸው። አገራችን ከፍተኛ የችግር ረግረግ ውስጥ ነው ያለችውእንደ አገር በጥፋት ጎዳና ላይ እየሄድንበት ያለው ፍጥነትም እጅግ አስፈሪ ነው። ኢሕአዴግ አዳዲስና ተለዋዋጭ ነገሮችን ግምት ውስጥ ያስገባ የአስተዳደር ሥርዓት ለውጥ ሳይደርግ አመርቂ ውጤቶችን ለማስገኘት አይችልም ከዘመኑ እሳቤና ርዕዮት ጋር የሚጋጩ የአስተዳደር ጽንሰ ሐሳቦች ላይ ተተክ አገሪቱ ያሉባትን ወቅታዊ ችግሮች በቅጡ መረዳት አይችልም። በቅጡ ያልተረዳው ችግር ደግሞ መፍታት አይቻለም። ለዘመናችን የሚሆኑ መፍትሔዎችን በተፈላጊ ፍጥነት የሚያቀርቡ አዳዲስ ጽንሰ ሐሳቦች ያስፈልጉታል ከላይ የተጠቀሱት በዋናነት እንደ ፓርቲነቱ ኢሕአዴግን የሚመለከቱ ቢሆኑም ሌሎቻችንም እንደ ንቁም እንደ ፍዝም ተዋናይነታችን የየድርሻችን ማንሳታችን አይቀርም።  ቀጥሎ የምናያቸው ስድስቱ የድርጅታዊ ፊዚክስ መርሆች በአንድ ድርጅት ስጥ የሚገኝ ዓይነተ ብዙ ጉልበት ሁለንተናዊ ጥቅም ላይ እንዴት ይዋል? እንዴት ከዘመኑ ጋር ይራመድ? ለሚሉ ጥያቄዎች መልስ ያስገኛሉ

ስድስቱ መርሆች

ኢሕአዴግ ከውድቀት ተርፎ ተጠናክሮ መቀጠልን ካላመ፣ ራሱንም አገሪቱንም በዕድገት ጎዳና በፍጥነት ንቀሳቀስ ከፈለገ፣ በተሻለ ሁኔታ ለውጥን አቅዶ በተሳካ መንገድ ዕቅዱን በተግባር ለማዋል ካሰበ፣ ቀጥሎ አንድ በአንድ የሚዘረዘሩት ስድስቱን መርሆችን ማወቅ ይገባዋል።

መርሆ 1 ከሚራበት አካባቢ አኳያ አካባቢውን ለውጦና ራሱም ተለውጦ የማይቀጥል ድርጅት ሊኖር አይችልም

ድርጅቶች እርስ በርስ የተቆራኙ ብልቶችና የተያያዙ ንዑስ ሥርዓቶች ያሏቸው ውስብስብ ርዓቶች ናቸው። በአካባቢያቸው የሚገኝ ሁኔታን ይቀር፡፡ ይለውጣሉ። አካባቢያዊ ሁኔታዎች ግብረ መልስ ስለሚሰጡ ይለወጣሉ። ይህ ይሆን ዘንድ ግድ ነው፡፡ የፊዚክስ ግ ነውና ኢሕአዴግ የአራት ብሔራዊ ድርጅቶች ግንባር ነው። የየራሳቸው አካባቢ ያላቸው፡፡ በመልክዓ ምድራዊ አካባቢ ብቻ ያልታጠረ። ከጊዜ ጋር በየራሳቸውም በጋራ እንደ ግንባርም በለውጥ ደት ውስጥ ማለፋቸው የግድ ነው። አውቀው ይለውጡ ይለወጡ ሌላ ጥያቄ ሆኖ።

አንድ የሆነ ነገር በትክክል እንዴት እንደሚሠራ ለመረዳት ነገሩን በየብልቱ ፈታትቶ መበታተን ብቻ በቂ አይደለም። ነገሩን በተሳሰረ ወጥ ሥርዓትነት ዓውድ ማየት ስንችል የተሻለ መረዳት እንፈጥራለን እንዲያውም ‘ማንኛውም ርዓት ከብልቶቹ ድምር በላይ ነው’  የሚባለው። ይህ ነባራዊ ቅ ለፖለቲካ ድርጅትም ያስኬዳል። ብዙ ተቃዋሚዎች ሆን ብለውም ሆነ ሳያውቁ ኢሕአዴግን በታትነው ነው ማየት የሚፈልጉት። እንዲያውም ወሓት/ ኢሕአዴግ’ ሲሉ ወሓት’ የሚለው ላይ አጽንኦት ሰጥተው ነው ከላይ እንዳልኩት ኢሕአዴግ የየራሳቸው ታሪክ ፍላጎትና ጉልበት ያላቸው አራት ብሔራዊ ድርጅቶች ግንባር ነው።  በሚዮኖች የሚቆጠሩ ዕለታዊ ይወታቸውን ከግንባሩ በተለይም ከየብሔራዊ ድርጅቶቹ ጋር የሚያያዙ ካድሬዎችና አባላ ያሉት ግንባር ነው። አራቱ ድርጅቶች ከ27 ዓመታት በላይ አብረው ሲሩ አካባቢያቸውን ቀርዋል ግብረ መልስ ተቀብለዋል ሰጥተዋል። የድርጅቶቹ የውስጥ ትስስርም ሆነ ከማኅበረሰቡ ጋር ያላቸውን ትስስር በቅጡ የሚያሳይ መነጽር ላይ ተመርቶ የሚሰጥ ትንታኔ ያስፈልገናል። ኢሕአዴግን ውስብስብ እንደሆነ እንደ አንድ ተለዋዋጭ ሥርዓት መመልከት ስንጀምር ነው እንደ ሥርዓት እንዴት እንደሚሠራ ለማወቅ ጠቃሚ ግንዛቤ የምናገኘው ከውስጣዊና ከውጫዊ ነባራዊ ሁኔታ አንስናየው ኢሕአዴግ በተለያየ ጊዜ ራሱን ሲለዋውጥ እናየዋለን።

የኢትዮ ኤርትራ ጦርነት1993 ዓ.ም.ወሓት ክፍፍል1997 ዓ.ም. ምርጫ የአቶ መለስ ሞት ኢሕአዴግን በአንድም በሌላም መንገድ እንዲለወጥ አድርገውታል። ‘የማይለወጥ ነገር ለውጥ ብቻ ነው’ ከሚለው ዘመን ተሻጋሪ ቅ በተራሪ ተቃዋሚዎች ኢሕአዴግ የማይለወጥ አድርገው የሚያምኑ እስኪመስሉ ድረስ  ኢሕአዴግን ያሳብቃሉ ብለው ያሰብዋቸውን የቆዩ ክስተቶች ላይ ሲቸከሉ ይታያሉ። ለምሳሌ የ1967 ዓ.ም. ወሓት ‘ማኒፌስቶ’ ያነሳሉ አሁንም ድረስ ሁሉን ነገር የሚቆጣጠረው ወሓት  ነው ይላሉ። ሌሎቹ የኢሕአዴግ አባል ድርጅቶችን ቆሞ ቀር አድርጎ መቁጠር አለ።  እርግጥ ሆን ተብሎ ለፕሮጋንዳ በሌት የሚደረገው እንዳለ ሆኖ ለውጥ አምጪ ታክቲካዊና ስትራቴጂካዊ መንገዶችን በቅጡ ካለመለየት ጋር የሚያያዝ ምክንያትና መነሻ እንዳለውም መገንዘብ ያስፈልጋል።

በዋናነት ግን ኢሕአዴግ ራሱ በውስጥ ያሉት አባል ድርጅቶቹም ራሳቸውንና ሌላውን ብሔራዊ ድርጅት የሚያዩት እንደ ድሮው ነው? የማይለወጥመለወጥ ያለበት(ቸው) መለወጥ የሚገባው(ቸው) አድርገው ነው? ወይስ ያኔ 1983 ዓ.ም. ላይ እንደነበረ(ሩ) አድርገው ነው? እዚህ ላይ ለውጥ ስል ማንኛውም ይነት ለውጥ ማለቴ አይደለም። ለአገሪቱ ተግዳሮቶች ነባራዊ ሁኔታዎችና ለሕዝቡ መረታዊም ወቅታዊም ፍላጎት የሚመጠን አስቸኳይ የለውጥ ደት ላይ ያልገባ ኢሕአዴግ ዕጣ ፈንታው ከጨዋታ ውጪ መሆን ነው በድርጅታዊ ፊዚክስ መርሆ አንድ መሠረት።  

መርሆ 2መጀመሪያው የቴርሞዳይናሚክስ ሕግ ተገ የማይሆን ድርጅት ሊኖር አይችልም

ቴርሞዳይናሚክስን ሥነ ወበቅ ብለን እንያዘው። በመጀመሪያው የቴርሞዳይናሚክስ ሕግ ረት አንድ ሥርዓት ውስጥ በማንኛውም ጊዜ የሚኖረው የኃይል መጠን ነው። አንድ ድርጅት እንደ ርዓት ይወት ለመቀጠል በየጊዜው አዲስ ኃይል ያስፈልገዋል። አዲሱ ኃይል የሚገኘው ደግሞ ከእሱ ውጪ ከሆነው አካባቢ ነው። በፊዚክስ ግ መሠረት በድርጅቱ ውስጥ ያለው ኃይል በጊዜ ደት እየተመናመነ ሄዶ ድርጅቱን ህልው ሆኖ ከማይችልበት ደረጃ ያደርሰዋል። እንደሚታወቀው በ ዳራዊው ዓለም ሳይቀር የዕዋት በቀዳሚነት በነሱ መሠረትነት ደግሞ የእንስሳት (ሰውን ጨምሮ) ይወት እንዲቀጥል የሚያስችለው ውጫዊ የታዳሽ የኃይል ምንጭ ሐይ ስላለች ነው። በእምነት ዓለምም ቢሆን የአማኞች የእምነት ይወት የሚቀጥለው በቀጣይነት በሚያገኙት ውጫዊ የመንፈሳዊው ዓለም ኃይል ምክንያት ነው።

ከኢሕአዴግ አኳያ ስናየውኃይልማለት ሥልጣን፣ ኢኮኖሚያዊ አቅም ለሐሳብ ገበያ የሚያቀርበው አሸናፊ ሐሳብ ከሁሉም በላይ ደግሞ ሕዝባዊ ተቀባይነት ነው። በኢሕአዴግ ውስጥ ሊኖረው የሚችለው ዘርፈ ብዙ ኃይልም ቢሆን ውን ነበር ነውም። ስለዚህ ኢሕአዴግ በራሱ ውስጥ የነበረው ኃይል እስካሁን አምጥቶታል። ከአሁን በኋላ ግን ይወስደዋል ብዬ አላምንም። ከራሱ ድርጅታዊ ግቢ ውስጥ አድርገን ከማንወሰዳቸው ወይም መውሰድ ከሌለብን አካባቢዎች ነው ኢሕአዴግ አዳዲስ ዓይነ ብዙ ኃይል ፍሰቶች ማግኘት ያለበት፡፡ ህልው ሆኖ መቀጠል ከፈለገና ከተጠቀመበ ከእነዚህ አዳዲስ የኃይል ፍሰት ምንጮች መካከል በዋናነት ሕዝቡ፣ ሕገ መንግሥቱ፣ የሕግ ሥርዓቱ፣ ኢኮኖሚውየማኅበረሰቡ እሴቶች ጎች ባህሎች ወዘተ ናቸው። አዲስ የግንባሩ አወቃቀር (ለምሳሌ ወደ አንድ ወጥ ፓርቲነት መቀየር የካድሬ ርዓትን ማስቀረት) አዲስ የፌዴራል አወቃቀር (ለምሳሌ ቋንቋና ብሔር መሠረት ካደረገው ውጪ) አዲስ የተወካዮች ምክር ቤት ስብጥር (ለምሳሌ አሁን ኢሕአዴግ ከያዛቸው መቀመጫዎች ውስጥ ግማሽ ያህሉን ትቶ በአጭር ጊዜ ውስጥ በማሟያ ምርጫ አገር ውስጥ ያሉትን ጥርስ ባላቸው የተቃዋሚ ፓርቲዎች እንዲያዙ ማድረግ) አዲስ የካቢኔ ስብጥር  ወዘተ አዲስ የኃይል ምንጮች ናቸው።

ግንባሩም ሆነ ብሔራዊ ድርጅቶቹ ውስጣዊ አቅማቸው ወጥተው ከየአካባቢያቸው ጋር ከፍተኛ ትስስር ከፈጠሩ ኢሕአዴግ አዲስ የኃይል አቅርቦት ስለሚያገኝ የተሳካለት ለውጥ የማምጣት ዕድ ይኖረዋል ይህ ዓይነት ትስስር ከሌለ ደግሞ ግንባሩ አዲስኃይል አቅርቦት ስለማይኖረው፣ በበረሃማ ደሴት ውስጥ ያለምንም ምግብና ውኃ አቅርቦት የሚኖር ሰው ቢውል ቢያድር እንጂ መጥፋቱ፣ መሞቱ እንደማይቀርለት ሁሉ ኢሕአዴግም ከጨዋታ ውጪ መሆኑ አይቀርም በመርሆ ሁለት መሠረት

መርሆ 3 ሁለተኛው የቴርሞዳይናሚክስ ሕግ ተገዥነቱን አውቆ የማይንቀሳቀስ ማንኛውም ድርጅት ላፊ ጠፊ ነው

ሁለተኛው የቴርሞዳይናሚክስ ሕግ ሁሉም ነገር ከጊዜ በኋላ አፈር ድሜ እንደሚበላ ይነግረናል። አፈር ድሜ መብላቱ የሚመጣው ከዕድሜ ጋር እየጨመረ በሚመጣው ብትንነትና ፍርሰት (ኤንትሮፒ) ምክንያት ነው። የሰው ልጆችን ጨምሮ የማንኛውም ሥርዓት ሕይወት ለዚህ የማይቀር ሀቅ ተገዥ ነው። ማናቸውም ቢሆኑ ከዚህ ሊያመልጡ አይችሉምና። የሰው ልጅ እያረጀ ሲመጣ ሞቱ የሚፈጥነውም በዚህ ሕግ አስገዳጅነት ነው።

ከመፋት ለመዳን አንድ ድርጅት ያለው ኃይል ወይም ጉልበት የብትንነትና የፍርሰትን ኃይል ለመቆጣጠርና ለመመከት ማዋሉ ተፈጥሯዊ ነው። ከጊዜ ብዛት የፍርሰት ጉልበት እየጨመረ ሲመጣ ድርጅቱ ካለው ውስጣዊ ጉልበት የበለጠውን እጅ ለምከታ ወጪ ለማድረግ እየተገደደ ይመጣል። በዚህ ምክንያት ለድርጅቱ ውስጣዊ ግንባታና አዲስ አቅም ለመፍጠር ሊውል የሚገባውና የሚችለው ጉልበት በመጠንም በዓይነትም ውሱን እየሆነ ይመጣል። ለዚያ ነው ትልቅ ስኬትን ለማሳካት የሚያልም ድርጅት ከአንድ እስከ ሦስት የቀረቡትን መርሆችን ታሳቢ አድርጎ መንቀሳቀስ የሚያስፈልገው።

ኢሕአዴግም በቅጡ የተገኘ ብሎም በቅጡ የሚቀዳ አዲስ ኃይልና ጉልበት ከላይ ከመርሆ ሁለት ር ከተጠቀሱት ምንጮች ካላገኘ መበታተኑና መፍረሱ ሳይታለም የተፈታ ነው፡፡ በዚህ መርሆ መሠረት።

መርሆ 4 ድርጅቶች ህልውናቸውን በስኬት ማስቀጠል የሚችሉት አካባቢያቸውን በመለወጥና በመቅረ ነው። ይህ አካባቢ ላይ አዋጪ ተፅዕኖ ማሳደር እንደ ድርጅትበውስጡ እንዳሉት ክፍሎችና ንዑስ ክፍሎችም የሚከወን ነው

በፊዚክስ የጥናት መስክ አንድ ድብልቅልቁ የወጣ በሚታይበት ጊዜ ተገማች ባልሆነ ቅጥ እንዲሁ በነሲብ የሚንቀሳቀስ ጠባይ ያለው ይመስላል። በአስተውሎት ሲታይ ደግሞ ነሲባዊ የሚመስለው እንቅስቃሴ ድግግሞሽ ባላቸው ቅጦችና ኃይሎች የተዋቀረና የሚነዳ ሊሆን ይችላል። ድግግሞሾቹ ርዓቱ ወጥ ግዙፍ አካል ደረጃም ርዓቱ ንዑሳን ብልቶች ደረጃም ሊከሰቱ ይችላሉ። ማንኛውም ይነት ድርጅትም ድብልቅልቁ እንደ ወጣ ርዓት ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። በተመሳሳይ መነጽር ሲታይ ጠጋ ብሎ ለሚያጠናው በሁሉም የድርጅቱ እርከኖች የሚገኙ የተለያዩ ቅጦችና የውስጥ ኃይሎች አሉት። ከትንንሽ ራዎች እስከ ትልቁ የድርጅቱ መገለጫ ጠባይ ድረስ ያሉት ነገሮች የሚወሰኑት በእነዚህ ቅጦችና የውስጥ ኃይሎች ናቸው።

እዚህ ላይ መጠየቅ ያለባቸው ጥያቄዎች አሉ። ድርጅቱ ከእሱ ያለውን አካባቢ የሚቀርበትና የሚለውጥበት መንገድ ምን ይመስላል? ለአካባቢው በየጊዜው የሚሰጠው ምላሽስ ምን ይነት ነው? ድርጅቱ አባላቱን የበታች መወዋቅሩንና በአጠቃላይ ሙሉ ድርጅቱን የሚያስተዳድረው እንዴት ነው?

ለእነዚህ ጥያቄዎች የሚሰጡት መልሶች በአንድ ድርጅት ውስጥ መገኘት ያለባቸው አራት ቀዳማዊያን ኃይሎችን ለመተንተን ይጠቅማሉ። እነዚህ አራት ቀዳማዊያን ኃይሎች በድርጅቱ ውስጥ የሚንባረቁ ግለሰባዊም ሆኑ የጋራ ጠባዮች ምን ሊመስሉ እንደሚችሉ ይጠቁማ አራቱ ቀዳማዊያን ኃይሎች አምራች ኃይል አረጋጊ ኃይል ራ ፈጣሪ (አዲስ ነገር አግኚ) ኃይልና አንድ አድራጊ ኃይል ይባላሉ። እያንዳንዱ ቀዳሚዊ ኃይል በሆነ ጊዜና ቦታ ጎልቶ በሚታይ የጠባይ ቅጥ ራሱን የሚገልጽ ሲሆን ሁልጊዜ ግን አራቱም ራ ላይ መሆን አለባቸውከአራቱ ኃይሎች አንድ ወይም ከአንድ በላይ ኃይል ከድርጅቱ ከጎደለ ወይም ከተዳከመ፣ ድርጅቱ ውሎ አድሮ መጥፋቱ አይቀርም። በውስጡ መገኘት ስላለባቸው ነዚህ ኃይሎች ድርጅቱ የሚያዳብረው መረዳት በአጠቃላይ በድርጅቱ ሥርዓት ውስጥ እየተደረገ ያለን ማንኛውም ጉዳይ ከሥር ከመሠረቱ ለመረዳት ከመጥቀሙም በላይ፣ ተፈላጊውን ለውጥ በሚፈገው መጠንና ዓይነት እንዲሁም ወቅት ለማሳካት ይጠቅመዋል።

ኢሕአዴግ ውስጥ ከትጥቅ ትግ ጀምሮ ወደ ኒልክ ቤተ መንግሥት ከገቡ በኋላም በመጀመሪያዎቹ ዓመታት እነዚህ አራት ኃይሎች ራቸውን እየሩ የነበረ ይመስለኛል፡፡ ከራሱ ርዕዮተ ዓለም አኳያ። አሁን ላይ ቆመን ኢሕአዴግ በውስጤ አምራች ኃይል አለኝን? አረጋጊ ኃይልስ? ራ ፈጣሪ (አዲስ ነገር አግኚ) ኃይልስ? አንድ አድራጊ ኃይልስ? ብሎ ራሱን ቢጠይቅ የሚያገኘው መልስ ግልጽ መሰለኝ። ስለዚህ በዚህ መርሆ መሠረት የኢሕአዴግ ዕጣ ፈንታ ግልጽ ነው።

መርሆ 5 ማንኛውም ድርጅት በአካባቢው ላሉ ሁኔታዎች ተገዥ መሆኑን አውቆ ከተለዋዋጭ ሁኔታዎች ጋር ራሱን ማስማማት አለበት

በዘገምተኛ ለውጥ ዘዋሪ መርሆ መሠረት በአካባቢያቸው የሚፈጠሩ ተገዳዳሪ ሁኔታዎችን አሸንፈው ሕይወታቸውን የሚያስቀጥሉት ጠንካሮ ወይም ብልሆቹ አይደሉም ራሳቸውን ተለዋዋጭ ከሆነ አካባቢያቸው ጋር አስማምተውና አጣጥመው የሚኖሩት ናቸው ሳይከስሙ በሕይወት የመቀጠል አቅም የሚኖራቸው

ዚያ ነው አንድ ድርጅት የሚኖርበት ሥራ የሚያከናውንበትን አካባቢ በተሳሳተ መንገድ ካነበበ ትልቅ ስህተት የሚሆነው። አካባቢውን በተሳሳተ መንገድ ሲያነብ ለወትሮ ለድርጅቱ አዲስጉልበት ምንጭ ሊሆን የሚችለው አካባቢ በተቃራኒው ጉልበት አስጨራሽ ይሆንበትና ወደ መጨረሻው ውድቀት መግፋቱ አይቀርም ከውድቀት ለመዳን ድርጅቱ የሚራበት አካባቢ ሁልጊዜ በመቀየር ሒደት ላይ መሆኑን ተገንዝቦ ኑባሬውን አፅንቶ ከአዳዲሶቹ ሁኔታዎች ጋር ራሱን ጣጣም ይጠበቅበታል። የተሳካ ማስማማት ዕውን ማድረግ ደግሞ የድርጅቱ ቁሳዊና ኅሊናዊ ምርቶች ከድርጅቱ የመፈጸም አቅ ከአካባቢው ፍላጎት (ሕዝባዊ ገበያ ፍላጎት) ጋር ተመጋጋቢ ወይም ተደጋጋፊ አድርጎ ማስኬድን ይጠይቃል።  ኢሕአዴግ ከላይ እንዳልኩት በተለያየ ወቅት ራሱን የለወጠም ቢሆንም ያደረጋቸው ለውጦች (መለወጦች) አካባቢውን በተገቢ ሁኔታ ጊዜውን ጠብቆ ሳይዘገይ በማንበብ የተደረጉ ለውጦች  አይደሉም። ይልቁንም ኢሕአዴግ ብዙ የአገሪቱ ሁኔታዎች በተለዋወጡበት ጊዜ እንኳን ራሱን ከነባራዊ ሁኔታዎች ጋር ሲያጣጥም አናየውም። የኢሕአዴግ ሰዎች ይህ በሁኔታዎች ወይም ከሁኔታዎች ጋር አለመለወጥ ‘መስመር’ ብለው የሚጠሩትና እንደ ጥሩ ነገር የሚኮሩበት ጉዳይ ነው። በድርጅታዊ ፊዚክስ ይን ግን የዚህ ይነት ‘መስመር’ ብሎ አንድ ቦታ ላይ መቸከል ክሽፈት ነው። ለምሳሌ በወደብ ጉዳይ ላይ በኤርትራ ነክ ጉዳዮች ላይ፣ በኢትዮጵያ ብሔርተኝነት ላይ፣ ወዘተ ኢሕአዴግ ‘አልሰማም አማም’ የማለት ያህል ተቸክሎ በመቅረቱ ኢትዮጵያ ከፍተኛ ዋጋ ከፍላለች እየከፈለችም ነው።

መርሆ 6 ማንኛውም ድርጅት ለእንቅስቃሴ ሕጎች ተገዥ ነው

በፊዚክስ ሦስቱ የኒውተን የእንቅስቃሴ ሕጎች ተብለው የሚጠሩ ሕጎች አሉ። እነዚህ ጎች በመላው ሁለንታ የሚገኙ አካላት ከሚያደርጓቸው እንቅስቃሴዎች ጀርባ ያሉትን መሠረታዊ መርሆችን ይገልጣሉ። ሦስቱ ሕጎች ከማኛውም አካል መንቀሳቀስ ወይም አለመንቀሳቀስ ጋር ተያይዘው የሚፈጠሩ ፍዘት የሽምጠጣና የአ ግብ ጉዳዮች የሚተነትኑና የሚያብራሩ ናቸው። ከእነዚህ ሕጎች የምናገኘው መሠረታዊው ቁምነገር ማንኛውም ድርጅት የሚያደርገው ለውጥም ሆነ የሚያሳየው እንድርድረት ለመረዳት ይጠቅማል። ትንተናው ላይ ተመሥርተን የምንደርስበትን ማጠቃለያ ይዘን ደግሞ ድርጅቱ ላይ ሁለንተናዊ ለውጥ ለማምጣት መጠቀም እንችላለን ለምሳሌ ፍዘት ሕጉ መሠረት ማንኛውም ድርጅት የሆነ የለውጥ ኃይል የተለየ ነገር እንዲያደርግ ካላስገደደው በስተቀር፣ ለወትሮው የሚያደርገውን ነገር ብቻ እያደረገ ለመቀጠል መዳዳቱ አይቀርም የቆመ ድንጋይ የሆነ ኃይል ካልገፋው ቆ እንደሚቀረው ማለት ነው። ኢሕአዴግ ለ27 ዓመታት ልጣን ላይ ሲቆይ ከአንድ ዙር ፍዘት ወደ ሌላ ዙር ፍዘት ሲሸጋገር የመጣ ነው። በመል የሚፈጠሩ ውስጣዊም ውጫዊም ግፊቶች ያደረጉት ነገር ቢኖር አንድ ወጥ የፍዘት ጎዳና ላይ ብቻ እንዳይቆይ ነው። ኢሕአዴግ እንደ ድርጅት በውስጡ ያከማቸው ይነተ ብዙመጠነ ቁስ’ ግንባሩ ለውጥን እንዳያመጣ ገትሮ ለመያዝ መዳዳቱ ተፈጥሮ ነው። የአንድ ድርጅ የመፈጸም አቅሙም ሆነ ፍጥነቱ የሚወሰነው በውስጡ ያለውን መጠነ ስ በማስተዳደር አቅሙ ነው። በድርጅቱ የሚከወን ማንኛውም ድርጊት በመጠን ተመጣጣኝ የሆነ ግን ተቃራኒ/ተቃዋሚ የአ ግብር እንደሚያስከትል ጎቹ አንዱ የሚገልጠው ነገር ነው።

በቅርብ ዓመታት ደግሞ በአገሪቱ በተለያዩ ቦታዎች በተከሰቱት ች ምክንያት ኢሕአዴግ ለዓመታት ከሚገኝበት ወቅታዊ ፍዘት ወጥቶ የተወሰነ መነቃቃት ያለበት እንቅስቃሴ እንዲያሳይ ያደረገው ይመስላል። የዚህ መነቃቃት ዘላቂነትና አዛላቂነት የሚለካው ግን ከላይ ተቀመጡት አምስት መርሆች አንድምታ ጋር በጣምራ ሲታይ ነው። ኢሕአዴግ ስድስቱን መርሆች በቅንጅት አይቶ ራሱን መለወጥ ካልቻለ ዕጣ ፈንታው አዎንታዊ አይሆንም።

ማጠቃለያ

በሌክስ ሲስኒም ይሁን በይታ የድርጅታዊ ፊዚክስ መርሆች በተቻለ መጠን ነባሩ ፊዚክስ ሕጎች ጋር በቅርበት እንዲቆሙ ተደርገው ለፉም በሁለቱም መካከል የዓላማና የትርጓሜ ልዩነት እንዳለ ግን ማስመር ያስፈልጋል። ዋናው ልዩነት የሰዎች ስብስብ የሆኑት ኢሕአዴግን ጨምሮ ዓይነተ ብዙ ድርጅቶች የተፈጥሮ ፊዚክስ ከሚያጠናቸው የግ ዓለም አጥንትና ጉልጥምት ይበልጥ ውስብስብ መሆናቸው አንዱ ነው። ሲጀመር የሰዎች ስብስብ ስንል ብዙ የማይታወቁ ነገሮች አሉትና። እንደዚያ ሆኖ ድርጅቶችን ከማቅናት አኳያ ድርጅታዊ ፊዚክስ እንደ ማያ፣ እንደ መፈተሻ፣ እንደ መዳሰሻ ስንጠቀምበት የምናገኘው ግንዛቤ ከራሳችን ክህሎት፣ ልምድ፣ አቅም፣ ሀብትና የድጋፍ ሥርዓት ጋር በማቀናጀት የምንፈተሸውን ድርጅት የበለጠ ለመረዳት ያስችለናል የሚለው ነው ቁምነገሩ

የድርጅታዊ ፊዚክስ ፍተሻችን ማጠቃለያ ኢሕአዴግ የራሱንም የአገሪቱንም ዕጣ ፈንታ ማሳመር ካለበት የምር የሆነ ለውጥ ማድረግ አለበት የሚለው ነው። የምር ለውጥ እንዲመጣም ከምሁራን አቅም ካላቸው ታዋቂ ሰዎች አገር ውስጥ ካሉ የተቃውሞ ፖለቲካ ሰዎች ወዘተ የተውጣጡ ሰዎች ያሉበት የመማክርት ኮሚሽን አቋቁሞ ወደ ተግባር የሚቀየር ምክር መጠየቅ አለበት። በዙሪያችን ከበው ያሉት የኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች ከመቼውም ጊዜ በላይ አሰፍስፈው እየጠበቁ መሆኑን ግንዛቤ ውስጥ አገብቶ የመማክርት ኮሚሽኑን በአዋጅ በቋሚነት እንዲደራጅ ማድረግ ይገባዋል።

የምንገኘው ውስብስብ በሆነ ዓለም ውስጥ ነው። ዓለሙ ደግሞ በመረጃ ጎርፍ ተጥለቅልቋል፣ በመረጃ ናዳ ተዋክቧል።  አገራችን ሕዝቡ የሚያምንበት የመረጃ ክምር ፈታሽ፣ ተንታኝ አደራጅ ያስፈልጋታል። ከመረጃው ክምር ገለባውን ፍሬ የሚለይ አበጣሪ ሻታል ወጥ በሆነ መንገድ እውነተኛ መረጃዎችን እያደራጁ ለጥበብ መር አገራዊ ውሳኔዎች መወለጃ የሚሆን እንቁላልና ዘር የሚያሰናዱ ያስፈልታል።

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይጠብቅ።

ከአዘጋጁ፡- ጸሐፊው ከ19 ዓመታት በላይ በአውሮፓ፣ በቻይና እንዲሁም በካናዳ በየክረምቱም ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት በተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ያስተማሩ ሲሆን፣ በመደበኛነት ካናዳ ሚገኘው ዩኒቨርቲ ኦፍ ካልጋሪ ተባባሪ ፕሮፌሰር በመሆን በማስተማርና በምርምር ራ ላይ ይገኛሉ። በተጨማሪም በአዛላቂ ልማት ላይ የማማከር ራ ይራሉ። በአሁኑ ጊዜ ደቡብ አፍሪካ በሚገኘው የስቴሌንቦሽ ኢንስቲትዩቱት ፎር አድቫንስድ ስተዲስ ፌለው ሆነው በአፍሪካ የአዛላቂ መሠረተ ልማት ግንባታ ላይ ምርምር እያደረጉ ሲሆን፣ ጽሑፉ የእሳቸውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እየገለጽን፣ ጸሐፊውን በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ማግኘት ይቻላል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር...

የትግራይ ክልል የሽግግር አስተዳደር ምሥረታና የሰላም ስምምነቱ ሒደት

በትግራይ ክልል ጊዜያዊ የሽግግር መንግሥት ለመመሥረት ደፋ ቀና እየተባለ...

ጥራዝ ነጠቅነት!

ከሜክሲኮ ወደ ጀሞ እየሄድን ነው፡፡ የተሳፈርንበት አሮጌ ሚኒባስ ታክሲ...

አወዛጋቢነቱ የቀጠለው የአዲስ አበባ የጤፍ ገበያ

ሰሞኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጤፍ የተከሰተውን የዋጋ ንረት...