Sunday, April 2, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
- Advertisement -

ፌርማታ ፅሁፎች

…እጅህ የጣለው

ትኩስ ፅሁፎች

የሰማይ መላእክት ገደብ ሳለባቸው

ገፍቶም ሳት ብሏቸው ÷ ከቶም ይዞላቸው

ኪሩቤ ባይናቸው ÷ ገልጠው አሏዩዋቸው፤

ሱራፊም በእጃቸው ÷ ነቅሰው አለዩዋቸው፤

እንዳንተ ተክህኖ ÷ ዳስሶ ፈትቷቸው

አካሌን ተየእጁ ÷ ምንስ ሊያገኛቸው።

አባ! አባ! ባሉ ÷ አባ ብትኮናቸው

መንጋህ በበረቱ ÷ በሰበሰባቸው

የበግ ለምድ ለባሽ ÷ ተኵላም አይነጥቃቸው።

ባለ ወርቁ ቅብዕ ÷ ሐውልተ ስምዕህ

ጀርባውን አዙሮ ÷ ለመቅደሱ ደንብ፤

ከቅዱሱ ማዕድ ÷ መዘጋጃ ቤት

ሕዝቡ ኹሌ ይራብ ÷ ቆሞ ታጠገብ።

የብርሃን ጸዳል ከሚፈስበት

በስተ ምዕራብ ዞሮ ÷ ለትንግርት ቢያዩት፤

ከመቅደሱ ርቆ ÷ የቆመው ሐውልት

ጀርባው በኋላዉ ÷ አዝሏል መልእክት።

በትረ ኃይሉን ይዞ ÷ ግራ ዘሙ እጅ

ዓለሙን ሲገዛ ÷ ሲነዳ እጅ በእጅ

እጅህ የጣለውም ÷ ይነሣ በአዋጅ፤

ሳለ ምልክቱ ÷ ምን ጊዜም በደጅ።

                        ኃይለ ልዑል ካሣ

                      ጥር 24/2010 /

                                              አዲስ አበባ

- Advertisement -
- Advertisement -

ተጨማሪ ለማንበብ

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች