የቻይና ፖሊስ መኰንኖች አንድን ተጠርጣሪ መለየት የሚችል የዓይን መነጽር አድርገው መንቀሳቀስ ጀምረዋል፡፡ ሲሲቲቪን ተክቶ መሥራት የሚችለው መነጽሩ ገጽታን በሚለይ (ፊሻል ሪኮግኒሽን) ቴክኖሎጂ በመታገዝ የሚሠራ መሆኑን የዘገበው ቢቢሲ ነው፡፡ መነጽሩ በቻይና መንግሥት የመረጃ ቋቶች ጋር የተገናኘ ሲሆን፣ ተጠርጣሪዎችን ለይቶ የሚያወጣው ገጽታን በሚለየው ቴክኖሎጂው በመታገዝ ነው፡፡ አንድ ፖሊስ ከሕዝቡ መካከል አንድን ተጠርጣሪ ሲያገኝ የተጠርጣሪውን ምስል ለይቶ በማውጣት በመረጃ ቋቱ ጋር ካለው መረጃ ጋር ያስተያያል፡፡ የመረጃ ቋቱም የተጠርጣሪውን ስምና አድራሻውን ይሰጠዋል፡፡
የአገሪቱ የመገናኛ ብዙኃን እንደሚለው፣ ቴክኖሎጂው በሥራ ላይ እንደዋለ ሰባት ተጠርጣሪዎች የተያዙ ሲሆን፣ በሐሰተኛ መታወቂያ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ 35 ግለሰቦች እንዲገኙም አስችሏል፡፡ አዲሱን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ሥራው በይፋ የተጀመረው ዜንጉ በተባለችው ከተማ በባቡርና በአውሮፕላን የሚጓጓዙ ተሳፋሪዎችን በመከታተል ነው፡፡