Thursday, September 21, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊየኢትዮጵያና የአሜሪካ የመከላከያና የደኅንነት ሹማምንት ግንኙነታቸውን በአሜሪካ ገመገሙ

የኢትዮጵያና የአሜሪካ የመከላከያና የደኅንነት ሹማምንት ግንኙነታቸውን በአሜሪካ ገመገሙ

ቀን:

  አምስተኛው የኢትዮ አሜሪካ የሁለትዮሽ የመከላከያ ምክር ቤት በአሜሪካ ባደረገው ስብሰባ፣ አሜሪካ ለኢትዮጵያ የምታደርገውን የደኅንነት ድጋፍና ትብብር መገምገሙ ተሰማ፡፡

ስብሰባው ባለፈው ሳምንት ውስጥ በዋሽንግተን ለሦስት ተከታታይ ቀናት የተካሄዱ መሆኑን ከአሜሪካ ኤምባሲ የተገኘ መረጃ ያመለክታል፡፡ የኢትዮጵያን ልዑክ የመሩት የመከላከያ ሚኒስትሩ አቶ ሲራጅ ፈጌሳና የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታ ማዦር ሹም ጄኔራል ሳሞራ ዩኑስ ናቸው፡፡ በአባልነት ከተሳተፉት መካከል ደግሞ የመረጃ መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተሩ ብርጋዴር ጄኔራል ተክለ ብርሃን ወልደ አረጋይና ሌሎች የደኅንነት ኃላፊዎች ይገኙበታል፡፡

የአሜሪካን ልዑክ የወከሉት ደግሞ የአሜሪካ የአፍሪካ ዕዝ አዛዥ ጄኔራል ዴቪድ ሮድሪጌዝና በፔንታጎን የአፍሪካ ጉዳዮች ምክትል ጸሐፊ ሚስ አማንዳ ዶሪ ናቸው፡፡

የስብሰባው አጀንዳ በአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ያሉ የፀጥታ ጉዳዮችን መገምገምና የተናጠል መረጃዎችን መለዋወጥ እንደሆነ የኤምባሲው መረጃ ያመለክታል፡፡ በውይይቱ ወቅትም ትኩረት አግኘተው የነበሩት የየመን የደኅንነት ቀውስ፣ የሶማሊያና የደቡብ ሱዳን ወቅታዊ ጉዳዮች መሆናቸውን የኤምባሲው መረጃ ያመለክታል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም አሜሪካ ለኢትዮጵያ የምታደርገው የመከላከያና የደኅንነት ትብብር ግምገማ እንደተካሄደም ከመረጃው ለማወቅ ተችሏል፡፡ በዚሁ ወቅትም የአሜሪካ ጂኦ ስፓሻል የደኅንነት ኤጀንሲና የኢትዮጵያ የመረጃ መረብ ደኅንነት ኤጀንሲ መሠረታዊ መረጃዎችን ለመለዋወጥና ትብብር ለማድረግ ስምምነት ፈርመዋል፡፡

የጅኦ ስፓሻል መረጃዎች ማለት ከአየር ላይ ወይም ከሳተላይት በመሬት ላይ የሚገኙ መረጃዎችን መሰብሰብና መተንተን ነው፡፡

ጂኦ ስፓሻል መረጃዎች የማዕድን ሀብቶችን ለማወቅና ለግብርናና ለመሳሰሉት ጥቅም የሚሰጥ ሲሆን፣ በኢትዮጵያ በኩል ይህንን እንዲሠራ ኃላፊነት የተሰጠው የኢትዮጵያ ካርታ ሥራዎች ኤጀንሲ ነው፡፡ ይሁን እንጂ የመረጃ መረብ ደኅንነት ኤጀንሲም የጂኦ ስፓሻል ኢንተለጀንስ ሥራ የማከናወን ኃላፊነት በአዋጅ ተሰጥቶታል፡፡

ይህም ማለት ከሳተላይት ወይም ከአየር ላይ በመሬት የሚከናወኑ እንቅስቃሴዎችን ለደኅንነት ሲባል የመከታተልና የመተንተን ኃላፊነት ተሰጥቶታል፡፡ በሁለቱ ተቋማት መካከል የሚታየውን የኃላፊነት መጣረስ ለማስተካከልም የማሻሻያ ሥራ በመሥራት ላይ መሆኑን ከዚህ ቀደም መዘገባችን ይታወሳል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ኮሚሽን ሪፖርት ምን ይዟል?

ለአሜሪካ ድምፅ አማርኛ ዝግጅት የስልክ አስተያየት የሰጡ አንድ የደንበጫ...

መንግሥት በአማራ ክልል ለወደሙ የአበባ እርሻዎች ድጋፍ እንዲያደርግ ተጠየቀ

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአማራ ክልል የተፈጠረው ግጭትና አለመረጋጋት በቢዝነስ...

አምናና ዘንድሮ!

እነሆ መስከረም ጠብቶ በአዲስ መንፈስ ተሞልተን መንገድ ጀምረናል። ‹‹አዲስ...