Thursday, June 8, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትየምሥራቅ አፍሪካ ‹‹ፉት ቦል ኔት›› ውድድር በሱዳን ካርቱም ይካሄዳል

የምሥራቅ አፍሪካ ‹‹ፉት ቦል ኔት›› ውድድር በሱዳን ካርቱም ይካሄዳል

ቀን:

ዕድሜያቸው ከ17 ዓመት በታች ታዳጊ ሕፃናትና ተማሪዎች የሚሳተፉበት የምሥራቅ አፍሪካ ‹‹ፉት ቦል ኔት›› የተሰኘ ውድድር በሱዳን ካርቱም ከግንቦት 28 እስከ 30 ቀን 2007 ዓ.ም. ድረስ ይካሄዳል፡፡ ኢትዮጵያ፣ ሱዳን፣ ኤርትራና ሶማሊያ ተሳታፊ አገሮች መሆናቸው ታውቋል፡፡

‹‹ፉት ቦል ኔት›› ከመደበኛው የእግር ኳስ ለየት እንደሚል፣ ዋነኛ ዓላማውም በታዳጊ ሕፃናት መካከል ውድድርን ወይም ፉክክርን ማዕከል አድርጎ የሚዘጋጅ እንደሆነም የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ አስታውቋል፡፡ እንደ መግለጫው፣ ተሳታፊ አገሮችና አካላት መቻቻልን፣ ትጋትንና መከባበርን፣ ለማጎልበት በሚል በኢትዮጵያ የኦሊምፕአፍሪካና በሱዳን ኦሊምፒክ ኮሚቴ ትብብር የተዘጋጀ እንደሆነ ጭምር አስታውቋል፡፡

ውድድሩ ከተለመደው የእግር ኳስ ጨዋታ የሚለይበት ባህሪ እያንዳንዱ ተወዳዳሪ ቡድን በስድስት ወንዶችና በአራት ሴቶች ተደራጅቶ መከናወኑ እንደሆነም ተገልጿል፡፡ በውድድሩ ለየት ያለ ክህሎትና ብቃት የሚያሳዩ ለሁለት ታዳጊ ሕፃናትና ወጣቶች ነፃ የትምህርት ዕድል እንደሚመቻችላቸውም በመግለጫው ተካቷል፡፡

በውድድሩ ኢትዮጵያን ወክለው የሚሳተፉ ታዳጊዎች በቢሾፍቱ ከተማ ከሚገኙ 12 የመጀመርያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች የተወጣጡ ተማሪዎች ሲሆኑ፣ ተወዳዳሪዎቹም ቀደም ሲል የ‹‹ፉት ቦል ኔት›› ጽንሰ ሐሳብና አተገባበር ሥልጠና የወሰዱ መሆናቸውን ጭምር ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴው አስታውቋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ከቀጣዩ ዓመት በጀት ውስጥ 281 ቢሊዮን ብሩ የበጀት ጉደለት ነው ተባለ

ለቀጣዩ በጀት ዓመት ከቀረበው 801.65 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ በጀት...

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከተለመደው አሠራር ወጣ ያለውን ‹‹የወደፊት ግብይት›› ሥርዓት በይፋ አስጀመረ

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከተለመደው የማገበያየት ተግባሩ ወጣ ያለና በኢትዮጵያ...

የባንክ ማቋቋሚያ መሥፈርት እንደሚጠነክር ሚኒስትሩ ተናገሩ

 ባንኮች ስለውህደት እንዲያስቡም መክረዋል በኢትዮጵያ ውስጥ ባንክ ለማቋቋም የሚያስፈልገው መሥፈርት...