Friday, June 2, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊሚድሮክ አጥሮ የያዛቸው 11 ቦታዎች ካርታ እንዲመክን ተወሰነ

ሚድሮክ አጥሮ የያዛቸው 11 ቦታዎች ካርታ እንዲመክን ተወሰነ

ቀን:

  • ውሳኔውን ተግባራዊ ለማድረግ የመንግሥት ውሳኔ ይጠበቃል

በሳዑዲ ዓረቢያ በእስር ላይ የሚገኙት ሼክ መሐመድ አል አሙዲ በኩባንያዎቻቸው ተመዝግበው ለዓመታት ታጥረው የተቀመጡ 11 ቦታዎች ካርታ እንዲመክን፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ ውሳኔ፣ በከተማው አስተዳደር ካቢኔና በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ይሁንታ ካገኘ ተፈጻሚ እንደሚሆን ታውቋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ ሥር የሚገኘው የመሬት ባንክና ማስተላለፍ ጽሕፈት ቤት፣ ባለፈው ዓመት መጨረሻ 120 ለሚሆኑ ፕሮጀክቶች የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ በመስጠት የሊዝ ውል ማሻሻያ በማድረግ የግንባታ ማስጀመሪያ ቀን አራዝሞ ነበር፡፡

በዚህ መሠረት 66 ፕሮጀክቶች በተሰጣቸው ጊዜ ወደ ግንባታ ገብተዋል፡፡ ወደ ግንባታ ካልገቡት መካከል 16 ያህሉ ውላቸው የተቋረጠ ሲሆን፣ ከእነዚህ ውስጥ ሰባቱ የመንግሥት ተቋማት የያዟቸው 4.76 ሔክታር ስፋት ያላቸው ናቸው፡፡ የሚድሮክና የዲፕሎማቲክ ተቋማት 29 ቦታዎች የተጠቃለሉ መሆናቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ደጋፊ የሥራ ሒደት አስተባባሪ አቶ ንጉሥ ተሾመ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

አቶ ንጉሥ እንደገለጹት ጽሕፈት ቤቱ በሚድሮክ ኩባንያዎች የተያዙ 11 ቦታዎችና በዲፕሎማቲክ ተቋማት የተያዙ 18 ቦታዎችም ካርታቸው መክኖ ወደ መሬት ባንክ እንዲገባ ውሳኔ አሳልፏል፡፡ ነገር ግን የመጨረሻውን ውሳኔ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ በማየት የመወሰን ጉዳይ የከተማው አስተዳደር ነው ሲሉ አቶ ንጉሥ አክለው ገልጸዋል፡፡

በሚድሮክ ከተያዙ ቦታዎች መካከል መሀል ፒያሳ፣ ሜክሲኮ አደባባይ ከዋቢ ሸበሌ ሆቴል ጎንና ካዛንቺስ ከኢንተርኮንቲኔንታል ሆቴል አጠገብ የሚገኙ ቦታዎች ይገኙበታል፡፡

በአጠቃላይ ሚድሮክ በአዲስ አበባ ከተማ 54 ሔክታር ስፋት ያላቸውን 11 ቦታዎችን ለዓመታት አጥሮ ይዟል፡፡ በጥቅምት 2010 ዓ.ም. የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አባተ ስጦታው፣ የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትሩ ዓለማየሁ ተገኑ፣ እንዲሁም የሚድሮክ ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብነት ገብረ መስቀል በተገኙበት ጉብኝትና ውይይት ተካሂዶ ነበር፡፡

በወቅቱ አቶ አባተ ከዚህ በኋላ ሚድሮክ ወደ ግንባታ ካልገባ የሊዝ ውል ማሻሻያ እንደማይደረግ፣ ይልቁኑም ቦታው እንደሚነጠቅ ተናግረው ነበር፡፡

‹‹በአስተዳደሩ በኩል የነበሩ ችግሮች በሙሉ ተፈተዋል፡፡ ስለዚህ ሚድሮክ ወደ ግንባታ መግባት ይኖርበታል፤›› በማለት አቶ አባተ ገልጸው ነበር፡፡

አቶ አብነት በበኩላቸው፣ የነበሩ ችግሮች መፈታታቸውንና በቂ በጀት የተመደበ መሆኑም ጭምር በመግለጽ ወደ ግንባታ እንደሚገባ ተናግረው ነበር፡፡ ነገር ግን ምንም ዓይነት ግንባታ ባለመጀመሩ የመሬት ባንክና ማስተላለፍ ጽሕፈት ቤት የቦታዎቹ ካርታ እንዲመክን ወስኗል፡፡

ነገር ግን ይህ ውሳኔ በከተማው አስተዳደርና በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ይሁንታ ካላገኘ ተፈጻሚ እንደማይሆን ምንጮች ገልጸዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...