Thursday, March 30, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናበሻሸመኔ ማረሚያ ቤት በተነሳ ቃጠሎ የሰው ሕይወት አለፈ

በሻሸመኔ ማረሚያ ቤት በተነሳ ቃጠሎ የሰው ሕይወት አለፈ

ቀን:

በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ አርሲ ዞን ሻሸመኔ ከተማ ውስጥ በሚገኘው የምዕራብ አርሲ ዞን ማረሚያ ቤት ዓርብ የካቲት 9 ቀን 2010 ዓ.ም. ከጠዋቱ አንድ ሰዓት አካባቢ በተነሳ የእሳት ቃጠሎ፣ የአንድ ታራሚ ሕይወት ሲያልፍ በሦስት ታራሚዎች ላይ ጉዳት ደረሰ፡፡

የማረሚያ ቤቱ በርካታ ማደሪያ ክፍሎች በእሳት መውደማቸው ተመልክቷል፡፡ የሻሸመኔ ከተማ ፀጥታና አስተዳደር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ናዶ አምቦ የቃጠሎውን መንስዔ በተመለከተ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ታራሚዎች መንግሥት ስለሌለ ከማረሚያ ቤት ማምለጥ እንችላለን በማለት ያስነሱት ቃጠሎ ነው፡፡

‹‹ሆን ተብሎ በተነሳው ቃጠሎ የአንድ ታራሚ ሕይወት ሲያልፍ፣ በሦስት ታራሚዎች ላይ ደግሞ ጉዳት ደርሷል፤›› ያሉት አቶ ናዶ፣ ‹‹የማረሚያ ቤቱ በርካታ ክፍሎች በእሳት ጋይተዋል፤›› ብለዋል፡፡

ኃላፊው ጨምረው እንደገለጹት፣ ታራሚዎቹን ወደ ሌላ ቦታ ማዛወር ሳያስፈልግ እዚያው ባሉበት እንዲሸጋሸጉ እየተመቻቸ ነው፡፡

የምዕራብ አርሲ ዞን አስተዳደር መቀመጫና የአካባቢው የንግድ ማዕከል የሆነችው ሻሸመኔ ከተማ፣ ባለፈው ሳምንት ከተቀሰቀሰው አመፅ ወጥታ መረጋጋት ላይ እያለች፣ የማረሚያ ቤቱ ቃጠሎ ዓርብ ማለዳ ላይ መከሰቱ ነዋሪዎችን አስደንግጦ ነበር፡፡

አቶ ናዶ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ባለፈው ዓርብ በሻሸመኔ ሁሉም የንግድ ቤቶች ተከፍተው ሥራ በመጀመራቸው የቀድሞው ሰላማዊው እንቅስቃሴ ቀጥሏል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

[የምክር ቤቱ አባል ላቀረቡት ጥያቄ በተሰጣቸው ምላሽ አቤቱታቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር ትክክል ነው? ምነው? ምክር ቤቱም ሆነ...

የጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ትኩሳት

ቅዳሜ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም. በጉራጌ ዞን ወልቂጤ...

አይ የእኛ ነገር!

የዛሬው ጉዞ ከጀሞ ወደ ፒያሳ ነው፡፡ መንገዱ ለሥራ በሚጣደፉ፣...

የዓለም ኢኮኖሚ መናጋት ለወቅታዊው የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ ችግር ምክንያት ነው?

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ባለፈው ማክሰኞ መጋቢት 16...