Sunday, April 2, 2023
- ማስታወቂያ -
- ማስታወቂያ -

የንግድ ባንክ ጁባ ቅርንጫፍን በመመዝበር የተጠረጠሩ ስምንት ሰዎች ላይ ክስ ተመሠረተ

- ማስታወቂያ -

ተዛማጅ ፅሁፎች

የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ደቡብ ሱዳን (ጁባ) ቅርንጫፍን በመመሳጠር መዝብረዋል ብሎ በጠረጠራቸው ሠራተኞች ላይ ሰኔ 9 ቀን 2007 ዓ.ም. ክስ መሠረተ፡፡

የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ ወንጀል ችሎት ክሱን የመሠረተው፣ በስምንት የቅርንጫፉ ሠራተኞች ላይ መሆኑ ታውቋል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ በቅርንጫፍ ባንኩ በኃላፊነትና በተለያዩ የሥራ መደቦች ላይ ሲያገለግሉ የነበሩ ናቸው፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ሰኔ 10 ቀን 2007 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡

የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ግለሰቦቹን የጠረጠራቸው እርስ በእርስ በመመሳጠር ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ ከጁባ ቅርንጫፍ ንግድ ባንክ ለግል ጥቅማቸው አውለዋል በሚል ነው፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ በኢትዮጵያ ምርት ገበያ የተለያዩ ቅርንጫፎች የመጋዘን ሠራተኞችን በሙስና ወንጀል በመጠርጠር ምርመራ ላይ መሆኑ ታውቋል፡፡

የተጠረጠሩት ሠራተኞች በተለያዩ የምርት ገበያው ስድስት መጋዘኖች የ11 ሚሊዮን ብር ምርት ማጉደላቸውን ክሱ ያመለክታል፡፡

spot_img
- Advertisement -spot_img

የ ጋዜጠኛው ሌሎች ፅሁፎች

- ማስታወቂያ -

በብዛት ከተነበቡ ፅሁፎች