Thursday, September 21, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊበጋብቻ ምክንያት የተነሳውን የጎሳ ግጭት የክልሉ ፖሊስ በአስቸኳይ እንዲቀርፍ ፌዴራል ፖሊስ አሳሰበ

በጋብቻ ምክንያት የተነሳውን የጎሳ ግጭት የክልሉ ፖሊስ በአስቸኳይ እንዲቀርፍ ፌዴራል ፖሊስ አሳሰበ

ቀን:

በደቡብ ክልል በጋብቻ ምክንያት በሐዲቾና በወላቢቾ ጎሳዎች መካከል የተቀሰቀሰውን ከፍተኛ ግጭት፣ የክልሉ ፖሊስ በአስቸኳይ እንዲቀርፍና ጥፋተኞችን ለሕግ እንዲያቀርብ የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን አሳሰበ፡፡

የፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ሰኔ 17 ቀን 2007 ዓ.ም. ለደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን በጻፈው ደብዳቤ፣ የፌዴራል ፖሊስን ወደ አካባቢው ማሰማራት አግባብነት እንደሌለው፣ የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ሰላምና ፀጥታ ለማስፈን በተሰጠው ሥልጣንና ኃላፊነት ኅብረተሰቡ ተረጋግቶና ደኅንነቱ ተጠብቆ እንዲኖር ለማድረግ የሕዝብ አደራና ኃላፊነቱን እንዲወጣ አሳስቧል፡፡

በዚህ የጎሳ ግጭት ተሳታፊ የሆኑት ሕገወጥ ድርጊት ፈጻሚዎች ላይ ምርመራው ተጣርቶ ለሕግ እንዲቀርቡ፣ የተፈናቀሉ ዜጎችም ወደ ቀድሞ መኖሪያ ቤታቸው እንዲመለሱ እንዲደረግ አሳስቧል፡፡

በሒዲቾና በወላቢቾ ጎሳዎች መካከል ግጭቱ የተቀሰቀሰው ከግንቦት 1 ቀን 2007 ዓ.ም. ወዲህ ሲሆን፣ ምክንያቱ ደግሞ የሐዲቾ ጎሳ አባል የሆነ ግለሰብ ከወላቢቾ ጎሳ አባል ከሆነች አንዲት ግለሰብ ጋር በመጋባቱ ነው፡፡

ይህንን ጋብቻ ያልተቀበሉ የወላቢቾ ጎሳ አባላት፣ ‹‹እንዴት አናሳ ዘር ከእኛ ዘር ይጋባል?›› በማለት በአንድ ላይ በመነሳት በሐዲቾ ጎሳ አባላት ላይ ጥቃትና የንብረት ውድመት መፈጸማቸውን ከአካባቢው ለፌዴራል መንግሥት ተቋማት አቤት ለማለት ተወክለው የመጡ ግለሰቦች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

የወላቢቾ ነዋሪዎችን ቤቶችና ንብረቶች በማቃጠልና ያገኙትን በመደብደብ፣ በበርካታ ነዋሪዎች ላይ ጉዳት ከማድረሳቸው በተጨማሪ ሰዎችን መግደላቸውን ተወካዮቹ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

ጉዳዩን በተመለከተ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የወንዶ ገነት ወረዳ ፖሊስ ኃላፊ የተፈጠረው ግጭት በአሁኑ ወቅት መቀረፉን ገልጸው፣ የሞተ ሰው አለ መባሉን አስተባብለዋል፡፡

የፖሊስ ኃላፊው ይህንን ይበሉ እንጂ፣ የሐዲቾ ጎሳ አባላት በርካቶቹ እስካሁን ወደ መኖሪያቸው እንዳልተመለሱና አሁንም ሥጋት ውስጥ መሆናቸውን ተወካዮቹ ይናገራሉ፡፡ 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ኮሚሽን ሪፖርት ምን ይዟል?

ለአሜሪካ ድምፅ አማርኛ ዝግጅት የስልክ አስተያየት የሰጡ አንድ የደንበጫ...

መንግሥት በአማራ ክልል ለወደሙ የአበባ እርሻዎች ድጋፍ እንዲያደርግ ተጠየቀ

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአማራ ክልል የተፈጠረው ግጭትና አለመረጋጋት በቢዝነስ...

አምናና ዘንድሮ!

እነሆ መስከረም ጠብቶ በአዲስ መንፈስ ተሞልተን መንገድ ጀምረናል። ‹‹አዲስ...