Tuesday, October 3, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዝንቅ‹‹ላሙን ለኛ በረቱን ለእረኛ››

‹‹ላሙን ለኛ በረቱን ለእረኛ››

ቀን:

ከሥነ ቃል ዓይነቶች አንዱ ተረት ነው፡፡ ተራቹ ‹‹ተረት ተረት›› ሲል  መላሹ ‹‹የላም በረት›› ወይም ‹‹የመሠረት›› እያለ መመለሱ፣ አድማጭ ተረቱን ለማዳመጥ መስማማቱን መግለጹ ነው፡፡ ተራቹ በዚህ ብቻ አይቆምም፣ ወደ ተረቱ የሚዘልቀው ‹‹ላሙን ለኛ በረቱን ለእረኛ›› በማለት ነው፡፡

ተረት በሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል ቢኖርም አካሔዱ ግን እንደየብሔረሰቡ ትውፊት ይለያል፡፡ ይህ የተረት መንደርደርያ የተገኘው ከአዲስ አበባ ሰሜን ምሥራቅ 140 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከሚገኘው አንኮበር ነው፡፡ አንኮበሮች ተረትን እንደ ቁም ነገር ማስተላለፊያ ማስተማሪያ /መማማሪያ፣ ይቅርታን ማስተማሪያ ብልሃት አድርገው ይጠቀሙበታል፡፡

‹‹ነገር በምሳሌ፣ ጠጅ በብርሌ፣ መዝሙር በሃሌ›› እንዲሉ አንኮበሮች ፍየልን በለፍላፊነት፣ ጦጣን በብልጠት፣ ዝንጀሮን በቂልነት፣ ኤሊን በአዝጋሚነት፣ በግን በየዋህነት፣ ጅብን በሆዳምነት፣ አንበሳን በጀግንነት፣ ዶሮን በረባሽነት በመጠቀም ቤተሰቦቻቸውን ልጆቻቸውን ያስተምሩበታል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ተመድንና ዓለም አቀፋዊ ሕግን ከእነ አሜሪካ አድራጊ ፈጣሪነት እናድን!

በገነት ዓለሙ በእኔ የተማሪነት፣ የመጀመርያ ደረጃ ተማሪነት ጊዜ፣ የመዝሙር ትምህርት...

የሰላም ዕጦትና የኢኮኖሚው መንገራገጭ አንድምታ

በንጉሥ ወዳጅነው ፍራንክ ቲስትልዌይት የተባሉ አሜሪካዊ ጸሐፊ ‹‹The Great Experiment...

ድህነት የሀብት ዕጦት ሳይሆን ያለውን በአግባቡ ለመጠቀም አለመቻል ነው

በአንድነት ኃይሉ ድህነት ላይ አልተግባባንም፡፡ ብንግባባ ኖሮ ትናንትም ምክንያት ዛሬም...