Wednesday, October 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊየውኃና ፍሳሽ ባለሥልጣን 95 ባለሙያዎች ለመቅጠር ላወጣው ማስታወቂያ 13 ሺሕ ተወዳዳሪዎች አመለከቱ

የውኃና ፍሳሽ ባለሥልጣን 95 ባለሙያዎች ለመቅጠር ላወጣው ማስታወቂያ 13 ሺሕ ተወዳዳሪዎች አመለከቱ

ቀን:

በአዲስ አበባ ከተማን ንፁህ የመጠጥ ውኃ አቅርቦት አስተማማኝ ለማድረግ በርካታ ፕሮጀክቶችን በማካሄድ ላይ የሚገኘው የአዲስ አበባ ከተማ ውኃና ፍሳሽ ባለሥልጣን፣ 95 ባለሙያዎችን ለመቅጠር ላወጣው ማስታወቂያ 13 ሺሕ ተወዳዳሪዎች አመለከቱ፡፡

ባለሥልጣኑ ታኅሳስ 15 ቀን 2010 ዓ.ም. በአምስት የሥራ መደቦች 95 ባለሙያዎችን ለመቅጠር ባወጣው ማስታወቂያ መሠረት ምዝገባ ለማካሄድ፣ በርካታ ሥራ ፈላጊዎች መገናኛ አካባቢ የሚገኘውን የባለሥልጣኑ ዋና መሥሪያ ቤት አጥለቅለቀው ሰንብተዋል፡፡

ባለሥልጣኑ ለሲኒየር ኦዲት ኦፊሰርና ለኦዲት ኦፊሰር የመጀመርያ ዲግሪ ለያዙ ሁለት ዓመት የሥራ ልምድ ጠይቋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ መሐንዲስ (ለውኃ)፣ መሐንዲስ (ለፍሳሽ) እና የስታንዳርድ አፈጻጸም ምዘና ክትትል ኦፊሰር የመጀመርያ ዲግሪ እና ዜሮ ዓመት የሥራ ልምድ ጠይቋል፡፡

ባለሥልጣኑ የደመወዙን መጠን በማስታወቂያ ላይ ግልጽ ያደረገ ሲሆን፣ ከ10,022 እስከ 13,240 ብር ወርኃዊ ደመወዝ አቅርቧል፡፡

አንድ መቶ ላልሞሉ የሥራ መደቦች ከ13 ሺሕ በላይ ባለሙያዎች መሠለፋቸው ብዙም የተለመደ አይደለም ሲሉ፣ አንድ የባለሥልጣኑ የሥራ ኃላፊ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

የአዲስ አበባ ውኃና ፍሳሽ ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ አወቀ ኃይለ ማርያም ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ሥራውን ለማግኘት በርካታ ሰዎች ቀርበዋል፡፡

‹‹ምናልባት የደመወዙ መጠን የተሻለ ስለሆነ ሊሆን ይችላል፤›› ሲሉ አቶ አወቀ በርካታ ሰዎች ሊያመለክቱ የቻሉበትን ምክንያት ገልጸዋል፡፡

ለተመዝጋቢዎቹ ከዓርብ የካቲት 23 ቀን 2010 ዓ.ም. ጀምሮ ፈተና እንደሚሰጥ ታውቋል፡፡ የአዲስ አበባ ውኃና ፍሳሽ ባለሥልጣን ለከተማው ነዋሪዎች ንፁህ የመጠጥ ውኃ ለማቅረብ፣ ፍሳሽ ቆሻሻዎችንም በዘመናዊ መንገድ ለማስወገድ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በማካሄድ ላይ ነው፡፡ በቢሊዮን ብሮች በሚቆጠር በጀት እየተከናወኑ ያሉት ፕሮጀክቶች በመልካም አፈጻጸም ላይ ይገኛሉ ተብሏል፡፡

ነገር ግን ባለሥልጣኑ በተለይ በንፁህ ውኃ አቅርቦት በኩል የኤሌክትሪክ መቆራረጥ ከፍተኛ ተግዳሮት እንደሆነበት በተደጋጋሚ እየገለጸ ነው፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

[ክቡር ሚኒስትሩ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው በቴሌቪዥን የሚተላለፈውን ዜና በመገረም እየተመለከቱ አገኟቸው]

ምንድነው እንዲህ ቀልብሽን የሳበው? ስለሰላም ኖቤል ሽልማት ዜና እየተመለከትኩ ነበር። እና...

የወሎ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ መመሥረትና የአማራ ክልል ጥያቄ

አማራ የኢሕአዴግ አንዱ መሥራችና አጋር ከሆነው ብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ...

የሽንኩርት ዋጋ ሰማይ የነካበት ምክንያት ምንድነው?

ባለፉት ሁለትና ሦስት ሳምንታት የሸማቾችን ኪስ ካስደነገጡ መሠረታዊ ከሚባሉ...

የአዲስ አበባ ንግድ ምክር ቤት ኤግዚቢሽን ማዕከልን እንዲያስተዳድር የተሰጠው ኮንትራት ለምን ተቋረጠ?

በአዲስ አበባ ከተማ ለንግድ ትርዒት ዝግጅት ብቸኛ በመሆን የሚጠቀሰው...