Friday, September 29, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ኪንና ባህልለሙያው የተሰጠ ክብር

ለሙያው የተሰጠ ክብር

ቀን:

ሙዚቀኛ ዳዊት ይፍሩ ከወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ በቅርቡ የክብር ዶክትሬት አግኝቷል፡፡ የስመ ጥሩ ሮሃ ባንድ መሥራቾች አንዱ የሆነው ዳዊት፣ በኢትዮጵያ ሙዚቃ ጉልህ ስፍራ ከሚሰጣቸው ሙዚቀኞች ውስጥ ይጠቀሳል፡፡ የኢትዮጵያ ሙዚቀኞች ማኅበርን በፕሬዚዳንትነት የሚመራው ሙዚቀኛው፣ በተለይ ሮሃ ባንድ ውስጥ ሙዚቃ አቀናባሪ በነበረበት ወቅት ከ200 በላይ አልበሞች ላይ አሻራውን አሳርፏል፡፡ ከሙዚቀኛው ጋር ሮሃ ባንድን ከመሠረቱ ሙዚቀኞች መሀከል ጆቫኒ ሪኮና ሰላም ሥዩም ይጠቀሳሉ፡፡ ባንዱ ካጀባቸው ሙዚቀኞች ሙሉቀን መለሰ፣ መሐሙድ አህመድ፣ ሐመልማል አባተና ኩኩ ሰብስቤ ጥቂቱ ናቸው፡፡ የሮሃ ባንድ አባላት በ1986 ዓ.ም. የተበታተኑ ሲሆን፣ በቅርቡ ከአባላቱ ጥቂቱ ተሰባስበው ከዝነኛው ዳምፃዊ መሐሙድ አህመድ ጋር በኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር መድረክ ላይ መጣመራቸው ይታወሳል፡፡ ዳዊትን ጨምሮ እነዚሁ የሮሀ ባንድ አባላት የድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩን አልበም በማዘጋጀት ላይም ይገኛሉ፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአማራ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ

እሑድ ጠዋት መስከረም 13 ቀን 2016 ዓ.ም. የፋኖ ታጣቂዎች...

ብሔራዊ ባንክ ለተመረጡ አልሚዎች የውጭ አካውንት እንዲከፍቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈቀደበት መመርያና ዝርዝሮቹ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ አጠቃቀምንና ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮችን...

እነ ሰበብ ደርዳሪዎች!

ከሜክሲኮ ወደ ዓለም ባንክ ልንጓዝ ነው። ሾፌርና ወያላ ጎማ...