በጋምቤላ ከተማ የትራንስፖርት አገልግሎት የሚሰጡ ባጃጆች ዛሬ የካቲት 21 ቀን 2010 ዓ.ም. ጠዋት ጀምሮ አገልግሎት ማቆማቸውን የሪፖርተር ምንጮች ከስፍራው አስታውቀዋል፡፡ በዚህም ምክንያት የአካባቢው ነዋሪዎች በትራንስፖርት እጦት እንደተቸገሩ ተናግረዋል፡፡
የባጃጅ ሾፌሮቹ ሥራ ያቆሙት አላግባብ ከፍተኛ ግብር እንድንከፍል ተጥሎብናል በማለት ሲሆን፣ የከተማው አስተዳደር ከሾፌሮቹ ጋር ውይይት ለማድረግ በዝግጅት ላይ መሆናቸውን ምንጮች ከስፍራው ገልጸዋል፡፡