Wednesday, September 27, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ኪንና ባህልምን የት?

ምን የት?

ቀን:

‹‹ሳይኪና ኪዩፒድ›› እና ‹‹የቋንቋ መሠረታውያን›› ለንባብ በቁ

‹‹ሳይኪና ኪዩፒድ›› እና ‹‹የቋንቋ መሠረታውያን›› በቅርቡ ለንባብ የበቁ የአብነት ስሜ መጻሕፍት ናቸው፡፡ ‹‹ሳይኪና ኪዮፒድ›› አሥር ተረቶች፣ አራት መቶ እንቆቅልሾችና አንድ የእንግሊዝኛ ልቦለድ የያዘ መጽሐፍ ነወ፡፡ ጸሐፊው በተለያየ ወቅት ያነበባቸው እንዲሁም በልዩ ልዩ መድረኮች ላይ የተረካቸውን ታሪኮች የያዘው መጽሐፉ 411 ገጾች አሉት፡፡ ጸሐፊው በመግቢያው ላይ እንደጠቀሰው፣ በተለይ የመጽሐፉ መጠሪያ የሆነው ታሪክ ከዋናው በተለየ ኢትዮጵያዊ ቀለም ሰጥቶታል፡፡ ‹‹ተወዳጅ ተረቶች ለኢትዮጵያ ልጆች›› በሚል መሪ ቃል የሚጀምረው መጽሐፉ በ90 ብር ከ99 ሣንቲም ለገበያ ቀርቧል፡፡ ሌላው የአብነት መጽሐፍ ‹‹የቋንቋ መሠረታውያን›› ጋዜጠኞች፣ የሕዝብ ግንኙነት ባለሙያዎች እንዲሁም በቋንቋ፣ በፎክሎር፣ በባህል፣ በታሪክና በትርጉም ዙሪያ ለሚሠሩ ግለሰቦች ጠቀሜታ እንደሚኖረው በመግቢያው ተጠቁሟል፡፡ በ14 ምዕራፎች ቋንቋ ነክ ርእሰ ጉዳዮችን የሚዳስሰው መጽሐፍ 407 ገጾች አሉት፡፡ በ90 ብር  ከ99 ሣንቲም ለገበያ ቀርቧል፡፡

********

የመጽሐፍ ምርቃት

‹‹ባቡሩ ሲመጣ›› የተሰኘው የጋዜጠኛና ደራሲ አንተነህ ይግዛው የአጫጭር ልቦለዶች መድበል ሐምሌ 17 ቀን 2007 ዓ.ም. በ11፡30 በኢትዮጵያ ሆቴል ይመረቃል፡፡ 14 አጫጭር ልቦለዶች የያዘው መጽሐፉ 210 ገጾች አሉት፡፡ በ60 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡ ደራሲው በኢትዮጵያ ፕረስ ድርጅት፣ በአዲስ ዘመን ጋዜጣና በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ሠርቷል፡፡ የመጀመርያ መጽሐፉ ‹‹መልስ አዳኝ›› በ2003 ዓ.ም. ለንባብ መብቃቱ ይታወሳል፡፡ 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

በጦርነት የወደመውን የአክሱም አውሮፕላን ማረፊያ ለመጠገን ተቋራጮች ሊመረጡ ነው

ከፍተኛ ጉዳት ለደረሰበት የባህር ዳር አውሮፕላን ማረፊያ ተርሚናል ምትክ...

ለአደጋ መከላከልና ምላሽ ለመስጠት የሚያግዝ ቴክኖሎጂ በ300 ሚሊዮን ብር ወጪ ተግባራዊ ሊደረግ ነው

በአዲስ አበባ ከተማ የድንገተኛ እሳትና አደጋን ለመከላከልና በፍጥነት ምላሽ...

የመላው ሕዝባችን የአብሮነት ፀጋዎች ይከበሩ!

ሕዝበ ሙስሊሙና ሕዝበ ክርስቲያኑ የመውሊድ፣ የደመራና የመስቀል በዓላትን እያከበሩ...

ብሔራዊ ባንክ ኅብረተሰቡና ባንኮች በሐሰተኛ የገንዘብ ኖቶች እንዳይጭበረበሩ አሳሰበ

ሐሰተኛ የገንዘብ ኖቶችን በማሳተምና በማሠራጨት ግብይት ላይ ለማዋል ጥረት...