Wednesday, September 27, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናበእነ አቡበከር አህመድ ላይ የተላለፈውን ፍርድ የአሜሪካ የሃይማኖቶች ኮሚሽን ተቃወመ

በእነ አቡበከር አህመድ ላይ የተላለፈውን ፍርድ የአሜሪካ የሃይማኖቶች ኮሚሽን ተቃወመ

ቀን:

የአሜሪካ ዓለም አቀፍ የሃይማኖቶች ነፃነት ኮሚሽን በእነ አቡበከር አህመድ መዝገብ የተከሰሱ ግለሰቦች ላይ የተሰጠው የጥፋተኝነት ብይንና ቅጣት ተገቢነት የለውም አለ፡፡

ሐምሌ 27 ቀን 2007 ዓ.ም. የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቦሌ ምድብ ችሎት በተከሳሾቹ ላይ ከሰባት እስከ 22 ዓመታት ፅኑ እስራት መወሰኑን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

‹‹ተከሳሾቹ ወንጀለኞች ሳይሆኑ ሰላማዊ የሃይማኖት ነፃነት አቀንቃኞች ናቸው፤›› ያሉት የኮሚሽኑ ሰብሳቢ ዶ/ር ሮበርት ጆርጅ፣ ‹‹የክስ ሒደቱ የኢትዮጵያ መንግሥት የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾችንና ተቃዋሚዎችን ፀጥ ለማድረግ የፀረ ሽብርተኝነት አዋጁን መጠቀም መቀጠሉን ያሳያል፤›› ብለዋል፡፡

ኮሚሽኑ የአሜሪካ መንግሥት በጉዳዩ ላይ ተቃውሞውን እንዲያቀርብ ጥሪ አድርጓል፡፡ የኮሚሽኑ አባላት እ.ኤ.አ. በ2012 ኢትዮጵያን ሲጎበኙ የተከሳሾቹ የፍርድ ሒደት ችግሮች እንደነበሩበት መረዳታቸውን፣ ከእነዚህም መካከል አንዱ የእስር አያያዛቸው በሕግ መሠረት የማይከናወን እንደነበር አስታውሷል፡፡

በኮሚሽኑ መግለጫ ላይ መንግሥት አስተያየት እንዲሰጥ ጥረት ቢደረግም፣ የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት መግለጫውን እንዳላዩት ገልጸዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአማራ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ

እሑድ ጠዋት መስከረም 13 ቀን 2016 ዓ.ም. የፋኖ ታጣቂዎች...

ብሔራዊ ባንክ ለተመረጡ አልሚዎች የውጭ አካውንት እንዲከፍቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈቀደበት መመርያና ዝርዝሮቹ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ አጠቃቀምንና ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮችን...

እነ ሰበብ ደርዳሪዎች!

ከሜክሲኮ ወደ ዓለም ባንክ ልንጓዝ ነው። ሾፌርና ወያላ ጎማ...