Saturday, December 9, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትብሥራት ጋሻው ጠና ለዓለም አቀፉ ፌዴሬሽን አመራርነት ይወዳደራሉ

ብሥራት ጋሻው ጠና ለዓለም አቀፉ ፌዴሬሽን አመራርነት ይወዳደራሉ

ቀን:

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽንን በፕሬዚዳንትነት ይመሩ የነበሩት ወ/ሮ ብሥራት ጋሻው ጠና የወከላቸው የአማራ ክልል ከሥልጣናቸው ቢያነሳቸውም፣ የዓለም አቀፍ አትሌቲክስ ፌዴሬሽኖች ማኅበር ግን ለከፍተኛው የምክር ቤት አባልነት በዕጩነት አቀረባቸው፡፡ ዓለም አቀፉ ፌዴሬሸን ከነሐሴ 13 ቀን 2007 ዓ.ም. ጀምሮ ለሁለት ቀን በቤጂንግ (ቻይና) በሚያካሂደው 50ኛው ጠቅላላ ጉባኤ ለምክር ቤቱ ለሴቶች ከተያዘው ስድስት መቀመጫ አንዱን ለመቆናጠጥ ወ/ሮ ብሥራት ከ10 በአትሌቲክስ በተወዳዳሪነትና በአመራርነት ካሳለፉ ዕጩ እንስቶች ጋር እንደሚወዳደሩ ማኅበሩ በድረ ገጹ ዘግቧል፡፡ ከአፍሪካ አህጉር ከኢትዮጵያ ሌላ ሞሮኳዊቷ የሎስአንጀለስ ኦሊምፒክ 400 ሜትር መሰናክል አሸናፊ ናዋል ኢል ማውታዋኬል መታጨታቸው ታውቋል፡፡ ኬንያ ለምክትል ፕሬዚዳንትነትና ለምክር ቤት አባልነት አንድ፣ አልጀሪያ፣ ቱኒዚያ፣ ሴኔጋል፣ ቤኒን፣ ናይጀሪያ ደግሞ  አንድ አንድ ዕጩዎች አቅርበዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...