Sunday, March 26, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናየአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ቆይታ አንደሚያጥር ተስፋ አደርጋለሁ አሉ

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ቆይታ አንደሚያጥር ተስፋ አደርጋለሁ አሉ

ቀን:

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሬክስ ቲለርሰን ዛሬ የካቲት 29 ቀን 2010 ዓ.ም. ከኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ወርቅነህ ገበየሁ (ዶ/ር) ጋር በሰጡት መግለጫ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ምንም እንኳን ለስድስት ወራት የታወጀ ቢሆንም ጊዜውን መንግሥት ያሳጥረዋል ብለው እንደሚያምኑ ገለጹ፡፡

ዴሞክራሲ በኢትዮጵያ ገና 27 ዓመታት ማስቆጠሩንና በባህርይው ፈታኝ በመሆኑ ችግሮች ሊታዩ እንደሚችሉና ኢትዮጵያም አሁን ወሳኝ ወቅት ላይ እንደምትገኝ ገልጸዋል፡፡

‹‹ሰላማዊ የሆነ የሥልጣን ሽግግር እንዲኖር መንግሥት እየሠራ ያለውን ሥራ እናደንቃለን፤›› ያሉት ቲለርሰን፣ ‹‹የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የሚታዩ አለመረጋጋቶችን ለማርገብ ቢያግዝም በአንዳንድ ዜጎች ላይ የዴሞክራሲያዊና የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ሊያስከትል ይችላል፤›› ሲሉ ሥጋታቸውን ገልጸዋል፡፡

የፖለቲካ አመራር የሆኑና ጋዜጠኞች ከእስር መፈታታቸውን ቲለርሰን አድንቀዋል፡፡

ከአገራዊ ጉዳዮች በዘለለ በተለይ ሶማሌና ደቡብ ሱዳን ላይ ትኩረት ያደረጉ አኅጉራዊና ቀጠናዊ ጉዳዮችን ቲለርሰን ከኢትዮጵያ አቻቸው ጋር መወያየታቸውም ታውቋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ለፋይናንስ ዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የማፍራት የቤት ሥራን የማቃለል ጅማሮ

የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እያደገ ለመሆኑ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ  የግል...

የምድር ባቡርን የሚያነቃቃው የመንግሥት ውሳኔ

በኢትዮጵያ ወደብ አልባነት ላይ የተደመረውን የሎጀስቲክስ ችግር ለመፍታት ግዙፍ...

የፓርላማ አባላት ስለሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ግልጽ መረጃ የለንም አሉ

‹‹ሕወሓትን ለፍረጃ አብቅተውት የነበሩ ጉዳዮች በአብዛኛው መልክ ይዘዋል›› ሬድዋን...