- Advertisement -

ክብረ ወሰን በሆነ ዋጋ የመሬት ጨረታ ያሸነፈው ኩባንያ ውል ተፈራረመ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ15ኛው ዙር ሊዝ ጨረታ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ባወጣው ቦታ፣ በከተማው ታሪክ ከፍተኛውን የመጫረቻ ዋጋ ያቀረበው ኩባንያ የሚጠበቅበትን ክፍያ በመፈጸም ውል መፈጸሙ ታወቀ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ መርካቶ ይርጋ ኃይሌ የገበያ ማዕከል አካባቢ 242 ካሬ ሜትር ቦታ በሊዝ ጨረታ ለማስተላለፍ በወጣው ጨረታ፣ ስኬት ኢንተርናሽናል ኩባንያ በከተማው ታሪክ ከፍተኛ የመጫረቻ ዋጋ ማቅረቡን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

ስኬት ኢንተርናሽናል ለዚህ ቦታ በካሬ ማትር 355,550 ብር ያቀረበ ሲሆን፣ ይህ ዋጋ በዝዋይ ኢንተርናሽናል ትሬዲንግ ተይዞ ከነበረው ክብረ ወሰን የሰበረ ዋጋ በ50,555 ብር ብልጫ አለው፡፡

ስኬት ኢንተርናሽናል ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ከጠቅላላ ዋጋው 20 በመቶ ቅድሚያ በመክፈል፣ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ባንክና ማስተላለፍ ጽሕፈት ቤት ጋር ውል መፈራረሙ ታውቋል፡፡

ከስኬት ኢንተርናሽናል ጋር ተወዳድሮ ተሸናፊ የሆነው ኩባንያ ያቀረበው የመጫረቻ ዋጋ ምንም እንኳ አሸናፊ መሆን ባይችልም፣ በከተማው ታሪክ ትልቁ የመጫረቻ ዋጋ ነው፡፡

ሁለተኛ የወጣው የቲዘዘኒ አክሲዮን ማኅበር ለዚህ ቦታ 355 ሺሕ ብር በካሬ ሜትር አቅርቧል፡፡ ከዚህ ቦታ በመቀጠል በ15ኛው ዙር ከፍተኛ ዋጋ የቀረበው እዚያው አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የወጣ ቦታ ነው፡፡

- Advertisement -

ይህ ቦታ መርካቶ ቦምብ ተራ አካባቢ የሚገኝ ሲሆን፣ በ11ኛው ዙር ሊዝ ጨረታ ለውድድር ቀርቦ በወቅቱ በከተማው ታሪክ ከፍተኛ ዋጋ የቀረበለት ነበር፡፡

449 ካሬ ሜትር ስፋት ላለው ለዚህ ቦታ፣ ዝዋይ ኢንተርናሽናል ትሬዲንግ በካሬ ሜትር 305 ሺሕ ብር ቢያቀርብም፣ በወቅቱ ያቀረበው ይህ ከፍተኛ ዋጋ አነጋጋሪ በመሆኑና በኩባንያው ላይ ተፅዕኖ በመፍጠሩ የተወሰኑ የኩባንያው ባለአክሲዮኖች የቀረበው ዋጋ እነሱን የማይመለከት መሆኑን በማስታወቃቸው፣ አክሲዮን ማኅበሩ ውል ሳይፈጽም ቀርቷል፡፡ ይህ ቦታ በ15ኛው ሊዝ ጨረታ በድጋሚ ቀርቦ ዝዋይ ኢንተርናሽናል ትሬዲንግ ካቀረበው ዋጋ ዝቅ ቢልም ከፍተኛ የሚባል ዋጋ ቀርቦለት ነበር፡፡

ለዚህ ቦታ አንደኛ በመሆን በካሬ ሜትር 286,500 ብር ያቀረበው ኤቲኤኤ ኮንስትራክሽን ኩባንያ ነው፡፡ ነገር ግን ይህ ኩባንያ ምክንያቱ ለጊዜው ግልጽ ባይሆንም፣ እስካለፈው ዓርብ ድረስ ውል መግባት ቢኖርበትም ውል አለመፈጸሙ ታውቋል፡፡

ለዚህ ቦታ ሁለተኛ ተወዳዳሪ በመሆን በካሬ ሜትር 262,000 ብር ያቀረበው ያረፈደ ትሬዲንግ አክሲዮን ኩባንያ ነው፡፡

የአዲስ አበባ አስተዳደር አሸናፊ ኩባንያዎች ይፋ ከተደረጉበት አሥር የሥራ ቀናት ውስጥ ውል ካልፈጸሙ፣ ሁለተኛ ከወጡ ኩባንያዎች ጋር ይዋዋላል፡፡ ነገር ግን ከአሥር ቀናት በተጨማሪ የሦስት ቀናት ማስጠንቀቂያ ጊዜ የሚሰጥ በመሆኑ፣ በዚህ ሳምንት እስከ ረቡዕ ነሐሴ 22 ቀን 2007 ዓ.ም. ድረስ ኩባንያው የመዋዋያ ጊዜ እንዳለው የአስተዳደሩ ባለሙያዎች  አስረድተዋል፡፡

ነገር ግን ከረቡዕ በኋላ ውል ያልፈጸሙ አሸናፊ ተጫራቾች፣ ለተጠባባቂ ተወዳዳሪዎች ዕድላቸውን አሳልፈው እንደሚሰጡ መረጃዎች አመልክተዋል፡፡ የከተማው አስተዳደር ሰኔ 15 ቀን 2007 ዓ.ም. ያወጣው 15ኛው ሊዝ ጨረታ ከሐምሌ 15 እስከ ሐምሌ 17 ቀን 2007 ዓ.ም. ድረስ መከፈቱ ይታወቃል፡፡

ውጤቱ ነሐሴ 9 ቀን 2007 ዓ.ም. የተገለጸ ሲሆን፣ ውጤቱ ከተገለጸ በኋላ ባሉት አሥር የሥራ ቀናት ውል የፈጸሙት ግማሽ ያህል ተጫራቾች ብቻ መሆናቸው ታውቋል፡፡     

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

በተያዘው ወር መጨረሻ  አዲስ ፖስፖርትና ቪዛ  ይፋ ይደረጋል ተባለ

በውጭ አገር የሚታተመውን ፓስፖርትና አገሪቱ ለውጭ ዜጎች የምትሰጠውን ቪዛ በአዲስ ይዘትና ኅትመት በአገር ውስጥ ታትሞ በተያዘው ወር የካቲት 2017 ዓ.ም. ይፋ እንደሚደረግ የኢሚግሬሽንና ዜግነት...

በውጭ አገር ለሚሰጥ ሕክምና የአገር ውስጥ ተወካይ ኃላፊነት እንዲወስድ የሚያስገድድ ረቂቅ መመርያ ተዘጋጀ

የጤና ሚኒስቴርን ፈቃድ አግኝተው በውጭ አገሮች የሕክምና አገልግሎት ተቋማት የሚታከሙ ኢትዮጵያውያን፣ የሕክምና አገልግሎት ጥራት ደረጃ ጉድለት፣ የሕክምና ስህተት ወይም የሙያ ግድፈት ቢፈጸምባቸው፣ የውጭ ሕክምና...

በአማራ ክልል የአሽከርካሪዎች ዕገታን መደበኛ የሥራ ቦታ አድርጎ የሚንቀሳቀሰው መበራከቱ ተገለጸ

በአማራ ክልል ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣው የአሽከርካሪዎች ዕገታ በአሁኑ ወቅት ክፍት የሥራ ቦታ እየሆነ መምጣቱ ተነገረ፡፡ አሽከርካሪዎችን በማገት ከፍተኛ ገንዘብ የሚጠይቁና ሲያዙም በአግባቡ በሕግ...

የባሕር ዳርና ድሬዳዋ ኤርፖርቶች የሲቪል በረራዎች ቁጥጥር ስርዓታቸውን አሳደጉ

በኢትዮጵያ ከሚገኙት አራት ዓለም አቀፍ ኤርፖርቶች መካከል የሆኑት የባህር ዳርና የድሬዳዋ ኤርፖርቶች፣ የአየር በረራዎች ቁጥጥር ክፍሎች ከጥር ወር 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ማናቸውንም እስከ 25...

ኢትዮ ቴሌኮም አገልግሎቱን በርካሽ ዋጋ ማቅረቡ ከተወዳዳሪው ኩባንያ ቅሬታ እየቀረበበት መሆኑን አስታወቀ

ኢትዮጵያ ቴሌኮም ጉልህ የገበያ ድርሻ እያለው አገልግሎቱን በርካሽ ዋጋ ማቅረቡ ለተወዳዳሪው ኩባንያው ውድድሩን አስቸጋሪ ስላደረገበት፣ ‹‹መንግሥታዊ ኩባንያው ዋጋ እንዲጨምር መገደድ አለበት የሚል የቅሬታ ጥያቁ...

በአማራ ክልል በፀጥታ ችግር ምክንያት 39 ምድብ ችሎቶች ከአገልግሎት ውጪ መሆናቸው ተረጋገጠ

በስድስት ወራት 89 ዳኞች ሥራ መልቀቃቸው ተነግሯል የክልሉ ዳኞች ያለመከሰስ መብት ተጠበቀላቸው በአማራ ክልል በፀጥታ ችግር ምክንያት ከ221 ፍርድ ቤቶች 39 የዞንና የወረዳ ምድብ ችሎቶች አገልግሎት...

አዳዲስ ጽሁፎች

የጤናው ዘርፍ ባለፉት ስድሥት ወራት

የወባ በሽታ ከሰሃራ በታች በሚገኙ የአፍሪካ አገሮች ዋነኛ የጤናና የማኅበራዊ ቀውስ መንስዔ ነው፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት እ.ኤ.አ. በ2024 ያወጣው መረጃም 263 ሚሊዮን ሰዎች የወባ...

የአዲስ አበባ የኮሪደር ልማት በባለሙያ ዓይን

(በጎ ጎኖችና እርምት የሚፈልጉ ጉዳዮች) በዮሐንስ መኮንን በጥር ወር 2016 ዓ.ም. የአዲስ አበባ ዋና ዋና ኮሪደሮችን በማዘመን ከተማዋን ለነዋሪዎቿና ለጎብኚዎቿ ምቹ ያደርጋታል የተባለ ፕሮጀክት በ43 ቢሊዮን...

በልዩነት ውስጥ ሆነንም እስኪ እንነጋገር

በገነት ዓለሙ ዴሞክራሲ መብቶችና ነፃነቶች የሚሠሩበት የሕዝብ አስተዳደር ነው፡፡ ሰብዓዊ መብቶችንና ነፃነቶችን መኗኗሪ ያደረገ ሥርዓት ነው፡፡ እነዚህ መሠረታዊ መብቶችና ነፃነቶች በተፈጥሮ የተገኙ፣ ሰው በመሆናችን ብቻ...

ለጤናማ የትራፊክ ፍሰትና ለመንገድ ደኅንነት ቅጣት መጣል ብቻውን መፍትሔ አይሆንም!

በአዲስ አበባ ከተማ ለተሽከርካሪዎች ምቹ የሆኑ መንገዶችን እየተመለከትን ነው፡፡ ከአዳዲሶቹ መንገዶች ባሻገር አንዳንድ ነባር መንገዶች የማስፋፊያ ሥራ ታክሎባቸው አገልግሎት ላይ ውለዋል፡፡ ከኮሪደር ልማቱ ጋር...

የግጭት አዙሪት ውስጥ ሆኖ የአፍሪካ ማዕከል መሆን ያዳግታል!

የአፍሪካ ኅብረት 38ኛው የመሪዎች ጉባዔ በአዲስ አበባ ሲካሄድ ብዙ ትዝ የሚሉ ጉዳዮች አሉ፡፡ እጅግ በጣም አሰልቺ፣ ውጣ ውረድ የበዛበትና ታላቅ ተጋድሎ ተደርጎበት ከከፍተኛ ዲፕሎማሲያዊ...

አገሬ ምንተባልሽ – ልብ ያለው ልብ ይበል

በቶማስ በቀለ ይቺ አገራችን ብዙ ተብሎላታልም፣ ብዙ ተወርቶባታልም፣ አገሪቱ በቅኝ ያልተገዛች ብቸኛ አገር (ላይቤሪያን ጨምሮ) ከመሆኗ አኳያ የሚነገርላት ብዙ ጥሩና የሚገርሙ ነገሮች ያሉትን ያህል፣ ከረሃብ...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን