Tuesday, October 3, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 140 ሺሕ የቀበሌ ቤቶች እንዳሉት በቆጠራ አረጋገጥኩ አለ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 140 ሺሕ የቀበሌ ቤቶች እንዳሉት በቆጠራ አረጋገጥኩ አለ

ቀን:

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባካሄደው የቀበሌ ቤቶች ቆጠራ በስድስት ክፍላተ ከተሞች 140 ሺሕ ቤቶች እንዳሉት አረጋገጠ፡፡ በ1996 ዓ.ም. በተካሄደ ጥናት የከተማው አስተዳደር ከ150 ሺሕ በላይ የቀበሌ ቤቶች እንዳሉት ቢገለጽም፣ በአስተዳደሩ ዕውቅና ለመልሶ ማልማት ፕሮግራሞች የፈረሱ ቤቶች የመኖራቸውን ያህል በሕገወጥ መንገድ የግል ይዞታ የተደረጉ፣ ፈርሰው ከግል ይዞታ ጋር የተቀላቀሉ፣ ተስፋፍተው የተገነቡ፣ ወደ ግል ይዞታነት የተለወጡ በመኖራቸው በሕገጦች ላይ ዕርምጃ እንደሚወስድ ተገልጿል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቤቶች አስተዳደር ኤጀንሲ ባለፈው ዓመት የጀመረውን ቆጠራ በተያዘው በጀት ዓመት አጠናቋል፡፡ በዚህ ቆጠራ በመሀል አዲስ አበባ በሚገኙት ቂርቆስ፣ አራዳ፣ አዲስ ከተማ፣ ልደታ፣ ጉለሌና የካ ክፍላተ ከተሞች 140 ሺሕ ቤቶች መኖራቸው ተገልጿል፡፡ በአራቱ የማስፋፊያ ክፍላተ ከተሞች ቦሌ፣ ንፋስ ስልክ ላፍቶ፣ ኮልፌ ቀራኒዮና አቃቂ ቃሊቲ አነስተኛ ቁጥር ያላቸው የቀበሌ ቤቶች አሉ ተብሏል፡፡

የከተማው አስተዳደር ምን ያህል ቤቶች እንዳሉት በመረጃ ለማወቅ፣ መረጃውንም አውቆ ካርታ እንዲወጣላቸው፣ በሕገወጥ መንገድ በተያዙት ላይም ዕርምጃ ለመውሰድ መረጃ እንዲሰበሰብ ወስኗል፡፡

በዚህ መሠረት አስተዳደሩ ከ140 ሺሕ ትንሽ ከፍ የሚሉ ቤቶች እንዳሉት ያረጋገጠ ሲሆን፣ የቤቶች አስተዳደር ኤጀንሲ ምክትል ሥራ አስኪያጅና የቤት ርክክብና ማስተላለፍ ዋና ሥራ ሒደት መሪ ወ/ሮ አፀደ ዓባይ ለሪፖርተተር እንደገለጹት፣ ያሉት የቀበሌ ቤቶች ካርታ ይወጣላቸዋል፡፡

‹‹ለቀበሌ ቤቶቹ ካርታ እየተዘጋጀ ነው፡፡ ካርታው የሚዘጋጀው በኤጀንሲው ስም ነው፡፡ ለሕገወጥ ድርጊት በተጋለጡት ላይ ደግሞ የማስተካከያ ዕርምጃ ይወሰዳል፤›› ብለዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ተመድንና ዓለም አቀፋዊ ሕግን ከእነ አሜሪካ አድራጊ ፈጣሪነት እናድን!

በገነት ዓለሙ በእኔ የተማሪነት፣ የመጀመርያ ደረጃ ተማሪነት ጊዜ፣ የመዝሙር ትምህርት...

የሰላም ዕጦትና የኢኮኖሚው መንገራገጭ አንድምታ

በንጉሥ ወዳጅነው ፍራንክ ቲስትልዌይት የተባሉ አሜሪካዊ ጸሐፊ ‹‹The Great Experiment...

ድህነት የሀብት ዕጦት ሳይሆን ያለውን በአግባቡ ለመጠቀም አለመቻል ነው

በአንድነት ኃይሉ ድህነት ላይ አልተግባባንም፡፡ ብንግባባ ኖሮ ትናንትም ምክንያት ዛሬም...