Tuesday, November 28, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊየግብፅ ፖፕ ቴዎድሮስ ዳግማዊ ለመስቀል በዓል አዲስ አበባ ይገባሉ

የግብፅ ፖፕ ቴዎድሮስ ዳግማዊ ለመስቀል በዓል አዲስ አበባ ይገባሉ

ቀን:

የግብፅ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፖፕና ፓትርያርክ ቴዎድሮስ ዳግማዊ በመስቀል በዓል አከባበር ላይ ለመታደምና የአራት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት ለማድረግ፣ መስከረም 15 ቀን 2008 ዓ.ም. አዲስ አበባ ይገባሉ፡፡

የኮፕቲክ ፓትርያርክ ቴዎድሮስ አራት ቀናት በሚወስደው ቆይታቸው መስከረም 16 ቀን 2008 ዓ.ም. የሚከበረውን የመስቀል ደመራ በዓል ላይ ከመታደማቸው በተጨማሪ፣ ወደ አክሱምና ላሊበላ አቅንተው ታሪካዊና ሃይማኖታዊ ሥፍራዎችን እንደሚጎበኙም ታውቋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም በሚኖራቸው ቆይታ በአዲስ አበባ የሚገኙ የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰብ አባላትን፣ እንዲሁም ከኢትዮጵያ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናትና ከታዋቂ ግለሰቦች ጋር እንደሚነጋገሩ ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ ከፕሬዚዳንት ዶ/ር ሙላቱ ተሾመና ከጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ጋር ተገናኝተው እንደሚወያዩ፣ እስካሁን ግን የተረጋገጠ ነገር አለመኖሩን አክለው አብራርተዋል፡፡  

ፓትሪያርኩ የአዲስ አበባ ጉዟቸውን አስመልክቶ ከሳምንት በፊት ከግብፅ የውኃ ሀብት ሚኒስትር ሆሳም አል ሞጋሃዚ ጋር መነጋገራቸው የተዘገበ ሲሆን፣ በውይይታቸውም ወቅት ግብፅ በታላቁ የህዳሴ ግድብ ላይ ያላትን ጥያቄዎች አንስተው ከኢትዮጵያ ባለሥልጣናትና ከአቡነ ማትያስ ጋር ውይይት እንዲያደርጉ ሚኒስትሩ መጠየቃቸውና የመግባቢያ ሰነድ መፈራረማቸው ተዘግቧል፡፡

ፖፕ ቴዎድሮስ በበኩላቸው ለዚህ ጥያቄ በሰጡት ምላሽ፣ ሁለቱ ቤተ ክርስቲያናት ባላቸው ታሪካዊ ግንኙነት የተነሳ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በዚህ ረገድ እየተባበሯቸው እንደሆነና አስተዋጽአቸውም ከፍተኛ እንደሆነ ገልጸዋል በማለት ስታር አፍሪካ የተሰኘ ድረ ገጽ ላይ የወጣ ዘገባ ያትታል፡፡

የኢትዮጵያ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ባለፈው ጥር ወር ግብፅን ለስድስት ቀናት በይፋ በጎበኙበትና በካይሮ ፕሬዚዳንታዊ ቤተ መንግሥት ከፕሬዚዳንት አልሲሲ ጋር በተወያዩበት ወቅት፣ ፕሬዚዳንቱ የዓባይ ወንዝ ለኢትዮጵያውያን የልማት ምንጭ ቢሆንም ለግብፅ ግን ልማት ብቻ ሳይሆን የደም ሥር መሆኑን መናገራቸው ይታወሳል፡፡

አቡነ ማትያስም በበኩላቸው በጠንካራ ትስስር ላይ የተመሠረተው የሁለቱ አገሮች ግንኙነት፣ ከዓባይ የሚመነጭ ውኃ የማያቋርጥ የጋራ ሀብት በመሆኑ በፍትሐዊነትና በእኩልነት ተጠቃሚ የሚኮንበት ይሆናል ማለታቸውም አይዘነጋም፡፡

ፖፕ ቴዎድሮስ ዳግማዊ እ.ኤ.አ. በ1952 ማንሱራ በተሰኘ የግብፅ ከተማ የተወለዱ ሲሆን፣ በ1975 ከኤሌክሳንዳርያ ዩኒቨርሲቲ በፋርማሲ የመጀመሪያ ዲግሪ አግኝተዋል፡፡ ለጥቂት ዓመታት በመንግሥት ቁጥጥር ሥር የሚገኝ መድኃኒት ፋብሪካን ከአስተዳደሩ በኋላ፣ ቅዱስ ፒስሆግ የተባለ ገዳም በመግባት የሥነ መለኮት ትምህርት በማጥናት እ.ኤ.አ. በ1989 ተመርቀዋል፡፡

የአቡነ ሺኖዳ ሕልፈተ ሕይወትን ተከትሎ በአሁኑ ወቅት 118ኛው የግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ በመሆን ከሦስት ዓመት ወዲህ በማገልገል ላይ ይገኛሉ፡፡   

 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ለሲኒመር ትሬዲንግ አ/ማ አባላት በሙሉ የጠቅላላ ጉባኤ የስብሰባ ጥሪ

ለሲኒመር ትሬዲንግ አ/ማ አባላት በሙሉ የጠቅላላ ጉባኤ የስብሰባ ጥሪ ሲኒመር ትሬዲንግ...

የባህር በር በቀጣናዊ ተዛምዶ ውስጥ

በበቀለ ሹሜ መግቢያ በ2010 ዓ.ም. መጋቢት ማለቂያን ይዞ ዓብይ አህመድ በጠቅላይ...

ሥጋት ያስቀራል ተብሎ የሚታሰበው የጫኝና አውራጅ መመርያ

በአዲስ አበባ ከተማ በሕገወጥ መልኩ በመደራጀት ማኅበረሰቡ ላይ እንግልትና...

ማወቅ ወይስ አለማወቅ – ድፍረት ወይስ ፍርኃት?

በአሰፋ አደፍርስ ወገኖቼ ፈርተንም ደፍረንም የትም አንደርስምና ለአገራችን ሰላምና ክብር...