Friday, December 8, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትየእንግሊዙ እግር ኳስ ክለብ አርሴናል ከዳሽን ቢራ ጋር ለሦስት ዓመት በአጋርነት ለመሥራት...

የእንግሊዙ እግር ኳስ ክለብ አርሴናል ከዳሽን ቢራ ጋር ለሦስት ዓመት በአጋርነት ለመሥራት ተፈራረመ

ቀን:

የእንግሊዙ እግር ኳስ ክለብ አርሰናል ከዳሽን ቢራ ጋር ለሦስት ዓመት የሚቆይ ለዳሽን ቢራ ክለብ ቴክኒካዊ ድጋፍ ለማድረግ የአጋርነት ስምምነት ተፈራረመ፡፡

ታላላቅ አሠልጣኞችም ከክለቡ ወደ ኢትዮጵያ በማምጣት ከታዳጊዎች ጀምሮ አስፈላጊውን ሥልጠና በመስጠት እንደሚሠሩ ተገልጿል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘም የአርሰናል የቀድሞ ተጨዋቾች ወደ ኢትዮጵያ በማምጣት ልምዳቸው እንዲያካፍሉ መንገድ እንደሚፈጥሩም ተመልክቷል፡፡

መስከረም 12 ቀን 2008 ዓ.ም. በተፈረመው ስምምነት በኢንተርኮንቲኔንታል የተፈራረሙት ድርጅቶች በቀጣይ ሦስት ዓመታት ዳሽን ቢራና አርሰናል በቅርበት በመሥራት በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙትን የቢራ ደንበኞችና የአርሰናል ደጋፊዎች የሚያቀራርብ ሊሆን እንደሚችል በመግለጫው ላይ ተገልጿል፡፡

የአርሰናል የእግር ኳስ ክለብ ዋና የንግድ ተጠሪ ቪናይ ሼንካተሻም በመግለጫው ላይ ‹‹አርሰናል እግር ኳስ ክለብ በመላው አፍሪካና ኢትዮጵያ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ደጋፊ እንዳለው ይታወቃል፤›› ብለዋል፡፡

በዚህም መሠረት ለመጀመርያ ጊዜ ከዳሽን ቢራ ጋር እንደዚህ ዓይነት የአጋርነት ስምምነት በመፈራረማችን አስደስቶናል በማለት በመግለጫው ላይ አስታውቀዋል፡፡ በተጨማሪም የዳሽን ቢራ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዴቪሊን ሄን ወርዝ ‹‹በስምምነቱ ዳሽን ቢራም ሆነ አርሰናል እግር ኳስ ክለብ ተጠቃሚ እንደሆነና ኅብረተሰቡም የጋራ ጥቅም እንዲኖረው የሚያስችል ነው፤›› ብለዋል፡፡

በመጨረሻም ስምምነቱ በቀጣይነት በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን እግር ኳስ ለማሳደግ እንደሚሠራና ሁሉም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ክለቦች ከዚህ የአጋርነት ሥራ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተገልጿል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...