- Advertisement -

የእንግሊዙ እግር ኳስ ክለብ አርሴናል ከዳሽን ቢራ ጋር ለሦስት ዓመት በአጋርነት ለመሥራት ተፈራረመ

የእንግሊዙ እግር ኳስ ክለብ አርሰናል ከዳሽን ቢራ ጋር ለሦስት ዓመት የሚቆይ ለዳሽን ቢራ ክለብ ቴክኒካዊ ድጋፍ ለማድረግ የአጋርነት ስምምነት ተፈራረመ፡፡

ታላላቅ አሠልጣኞችም ከክለቡ ወደ ኢትዮጵያ በማምጣት ከታዳጊዎች ጀምሮ አስፈላጊውን ሥልጠና በመስጠት እንደሚሠሩ ተገልጿል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘም የአርሰናል የቀድሞ ተጨዋቾች ወደ ኢትዮጵያ በማምጣት ልምዳቸው እንዲያካፍሉ መንገድ እንደሚፈጥሩም ተመልክቷል፡፡

መስከረም 12 ቀን 2008 ዓ.ም. በተፈረመው ስምምነት በኢንተርኮንቲኔንታል የተፈራረሙት ድርጅቶች በቀጣይ ሦስት ዓመታት ዳሽን ቢራና አርሰናል በቅርበት በመሥራት በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙትን የቢራ ደንበኞችና የአርሰናል ደጋፊዎች የሚያቀራርብ ሊሆን እንደሚችል በመግለጫው ላይ ተገልጿል፡፡

የአርሰናል የእግር ኳስ ክለብ ዋና የንግድ ተጠሪ ቪናይ ሼንካተሻም በመግለጫው ላይ ‹‹አርሰናል እግር ኳስ ክለብ በመላው አፍሪካና ኢትዮጵያ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ደጋፊ እንዳለው ይታወቃል፤›› ብለዋል፡፡

በዚህም መሠረት ለመጀመርያ ጊዜ ከዳሽን ቢራ ጋር እንደዚህ ዓይነት የአጋርነት ስምምነት በመፈራረማችን አስደስቶናል በማለት በመግለጫው ላይ አስታውቀዋል፡፡ በተጨማሪም የዳሽን ቢራ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዴቪሊን ሄን ወርዝ ‹‹በስምምነቱ ዳሽን ቢራም ሆነ አርሰናል እግር ኳስ ክለብ ተጠቃሚ እንደሆነና ኅብረተሰቡም የጋራ ጥቅም እንዲኖረው የሚያስችል ነው፤›› ብለዋል፡፡

በመጨረሻም ስምምነቱ በቀጣይነት በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን እግር ኳስ ለማሳደግ እንደሚሠራና ሁሉም የኢትዮጵያ እግር ኳስ ክለቦች ከዚህ የአጋርነት ሥራ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተገልጿል፡፡

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

‹‹የፕሮዤ ተሰማ›› ፍሬ የሆነው የአፍሪካ ኦሊምፒክ ተቋም አኖካ እና ኢትዮጵያ ያልታጨችበት ምርጫ

በአሁኑ ወቅት ሃምሳ አራት የአፍሪካ ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎችን ባንድነት ያቀፈው የአፍሪካ ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማኅበር (አኖካ)፣ ለመጪው አራት ዓመታት የሚመሩትን ፕሬዚዳንትና ሥራ አስፈጻሚዎችን በመጋቢት...

ስያሜውን ብቻ ሳይሆን መሥፈርቱን ሳያሟላ የቆየው የጃንሜዳ ኢንተርናሽናል አገር አቋራጭ ሻምፒዮና

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ‹‹ጃንሜዳ ኢንተርናሽናል አገር አቋራጭ ሻምፒዮና›› በሚል ከአራት አሠርታት በፊት በአዲስ አበባ ከተማ ያስጀመረው ሩጫ ዘንድሮ 42ኛውን ሻምፒዮና ባለፈው እሑድ ጥር 25...

ከዓመታት በኋላ የተጀመረው የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ውድድር

ለስድስት ዓመታት ተቋርጦ የቆየው የታዳጊ ወጣቶች ምዘና ውድድር በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ሶዶ ከተማ ጥር 27 ቀን 2017 ዓ.ም. መካሄድ ጀምሯል፡፡ የባህልና ስፖርት ሚኒስቴር...

‹‹የዩኒቨርሲቲዎች ስፖርት  መቋረጥ ለኢትዮጵያ ስፖርት መዳከም ዓይነተኛ ምክንያት ሆኖ ቆይቷል›› አቶ ዓባይ ይሁንበላይ፣ የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች ስፖርት ማኅበር ፕሬዚዳንት

ቀደም ባሉት ዓመታት ትምህርት ቤቶች፣ ዩኒቨርሲቲዎችና ወታደራዊ ክፍሎች  ስፖርታዊ እንቀስቃሴዎች የሚዘወተሩባቸው ነበሩ፡፡ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴና በደርግ፣ በተወሰነ ደረጃ በኢሕአዴግ ዘመን ተቋማቱ ስፖርታዊ ኩነቶቹ በስፋት...

ለዓመታት ተቋርጦ የቆየው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የስፖርት ፌስቲቫል ሐሙስ ይጀምራል

በትምህርት ቤቶች፣ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና ልዩ ልዩ ወታደራዊ ክፍሎች ከሚደረጉ ስፖረታዊ ውድድሮች አገርን በብሔራዊ ደረጃ የሚወክሉ አትሌቶች የሚፈሩበት ሰፊ ዕድል እንደነበር መዛግብት ያስረዳሉ፡፡ በተቋማቱ...

ለስድስት ዓመታት ተቋርጦ የቆየው የታዳጊ ወጣቶች አገር አቀፍ የምዘና ውድድር ሊጀመር ነው

የአፍሪካን እግር ኳስ ከመሠረቱ አራት አገሮች አንዷ የሆነችው ኢትዮጵያ፣ በጥር ወር 1954 ዓ.ም. የአፍሪካ ዋንጫ ያነሳችበት ወቅት ብቸኛው ሆኖ እየተጠቀሰ ይገኛል፡፡ ከዚያን ጊዜ ወዲህ...

አዳዲስ ጽሁፎች

የኢትዮጵያ ልሂቃን የፖለቲካ ባህል ከዕልቂትና ከውድመት አዙሪት እንዴት እንውጣ?

(የመጨረሻ ክፍል) በሰለሞን ኃይለ ማርያም (ዶ/ር) ባለፈው ሳምንት ጽሑፌ ስለፖለቲካ ባህል ጽንሰ ሐሳብ፣ ከኢትዮጵያ የልሂቃን የፖለቲካ ባህል ውስጥ ስም ማጥፋትን፣ ተቀናቃኝን ማጥቃትንና የመደራደርና የሰጥቶ መቀበል ባህል...

ኢትዮጵያ የአፍሪካን አጀንዳ በተመለከተ ምን ያህል አስተዋጽኦ ማድረግ ትችላለች?

በታደሰ ሻንቆ ኢትዮጵያ ትርጉም ያለው አስተዋጽኦ ለማድረግ የአፍሪካን 2063 ግቦች አጣቅሳ የተለየ ትልም መንደፍ አያስፈልጋትም፡፡ የውስጥ ሰላሟን ከማስተማመን ጋር አሁን የተያያዘችውን የትስስርና የግስጋሴ ፖሊሲ በማጎላመስ...

‹‹በጠመንጃ ተያይዘን እንወድቃለን እንጂ አብረን አንቆምም›› ፊልሰን አብዱላሂ፣ የሆርን ፒስ ኢንስቲትዩት መሥራችና ዳይሬክተር

የቀድሞዋ የሴቶች፣ ወጣቶችና ሕፃናት ሚኒስትር ፊልሰን አብዱላሂ አሁን ደግሞ ሆርን ፒስ ኢንስቲትዩት የተባለ በሰላም ላይ የሚሠራ ሲቪክ ማኅበር መሥርተው በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛሉ፡፡ ይህ ተቋም...

ነዳጅ ለመቅዳት እስከ ዕኩለ ሌሊት መሠለፍ የሚያበቃው መቼ ነው?

ያለመታደል ሆኖ በተደጋጋሚ እያጋጠሙን ለሚገኙ አንዳንድ ችግሮች ዘላቂ መፍትሔ ለማበጀት እየተቸገርን ነው። በተደጋጋሚ ለሚገጥሙን ችግሮች ጨከን ብሎ መፍትሔ ማምጣት ያለመቻላችን በራሱ ችግሮችን ለመፍታት አቅም...

‹‹ሕወሓት ሲፈልግ መንግሥት ሲፈልግ ፓርቲ ወይም ሕዝብ ነኝ ማለቱን ትቶ እንደ አንድ የፖለቲካ ፓርቲ መንቀሳቀስ አለበት›› ጌታቸው አሰፋ (ፕሮፌሰር)፣ ፖለቲካ ተንታኝ

ምርጫ ቦርድ ለሕወሓት የሰጠውና እስከ የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ ባሉት ቀናት ጠቅላላ ጉባዔ እንዲያደርግ የሚያስገድደው ማሳሰቢያ ቀነ ገደቡ ነገ ያበቃል፡፡ የካቲት 11...

‹‹አክሱም የአፍሪካዊ ሥልጣኔ በጨረፍታ››

በሽብሩ ተድላ ይህች ጽሑፍ መጠነኛ አስተያየት የምታቀርበው "AKSUM A glimpse into an African civilization by Hailu Habtu/Zamra Press.2024" (እኔ ርዕሱን "አክሱም የአፍሪካዊ ሥልጣኔ በጨረፍታ" ብዬ...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን