Friday, September 29, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትየኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ወደ ቡርኪናፋሶ ያመራል

የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ወደ ቡርኪናፋሶ ያመራል

ቀን:

ዕድሜያቸው ከ20 ዓመት በታች ለዓለም የሴቶች እግር ኳስ ዋንጫ ማጣሪያውን እያደረገ የሚገኘው የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን፣ ከቡርኪናፋሶ አቻው ጋር ቅዳሜ መስከረም 22 ቀን 2008 ዓ.ም. ኡጋዱጉ ላይ ይጫወታል፡፡ የዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ማኅበር (ፊፋ) ቡርኪናፋሶ በነበረባት የውስጥ ችግር ምክንያት የሁለቱ አገሮች የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ላልተወሰነ ጊዜ እንዲራዘም አድርጐ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ በዚሁ ምክንያት የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ያለምንም ጨዋታ በዝግጅት ብቻ ከወር በላይ ቆይቷል፡፡

በመጀመሪያው ዙር የካሜሩን አቻውን በደርሶ መልሱ ጨዋታ ከሜዳው ውጪ
0 ለ 0፣ በሜዳው ደግሞ 2 ለ 1 በመርታት ለቅዳሜው ጨዋታ የበቃው የኢትዮጵያ ዕድሜያቸው ከ20 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን፣ ባልተረጋጋ ሁኔታ ውስጥ የሚገኘውን የቡርኪናፋሶ አቻውን በደርሶ መልስ ጨዋታ ማሸነፍ ከቻለ ከጋናና ከኢኳቶሪያል ጊኒ አሸናፊ ጋር ይገናኛል፡፡ ቡድኑ ሐሙስ መስከረም 20 ቀን 2008 ዓ.ም. ወደ ሥፍራው እንደሚያቀናም ይጠበቃል፡፡
 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአማራ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ

እሑድ ጠዋት መስከረም 13 ቀን 2016 ዓ.ም. የፋኖ ታጣቂዎች...

ብሔራዊ ባንክ ለተመረጡ አልሚዎች የውጭ አካውንት እንዲከፍቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈቀደበት መመርያና ዝርዝሮቹ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ አጠቃቀምንና ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮችን...

እነ ሰበብ ደርዳሪዎች!

ከሜክሲኮ ወደ ዓለም ባንክ ልንጓዝ ነው። ሾፌርና ወያላ ጎማ...