‹‹ስድስት ሚሊዮን አይሁዶች ከተፈጁ ሰባ ዓመታት በኋላ የኢራን መሪዎች አገሬን ለማውደም ተማምለዋል፡፡ ሕዝቤንም ለመፍጀት፡፡ እዚህ (ተመድ) የሚገኘውም አካል ሆነ እንዲያውም የየመንግሥታቱ እንደራሴዎች አንዳችም ነገር ትንፍሽ አላሉም፡፡››
የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ 70ኛ ዓመቱን እያከበረ ባለው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) ጠቅላላ ጉባኤ ላይ መስከረም 22 ቀን 2008 ዓ.ም. ኒው ዮርክ ተገኝተው ካደረጉት ንግግር የተወሰደ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከ31 ዓመት በፊት በተመድ የእስራኤል ቋሚ መልዕክተኛና አምባሳደር በነበሩበት ጊዜም በወቅቱ ኢራን እስራኤል ከመንግሥታቱ ድርጅት እንድትወገድ ያቀረበችው ሐሳብ መቃወማቸውን በንግግራቸው መክፈቻ ላይ አስታውሰዋል፡፡