Friday, September 29, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናየፌዴሬሽን ምክር ቤት የፌዴራልና የክልል መንግሥታት ግንኙነት ፖሊሲ ሊያወጣ ነው

የፌዴሬሽን ምክር ቤት የፌዴራልና የክልል መንግሥታት ግንኙነት ፖሊሲ ሊያወጣ ነው

ቀን:

መስከረም 24 ቀን 2008 ዓ.ም. አዲስ አፈ ጉባዔ በመምረጥ አምስተኛ ዘመን ሥራውን የጀመረው የፌዴሬሽን ምክር ቤት በሁለተኛ ቀን ውሎው፣ በፌዴራልና የክልል መንግሥታት መካከል ሊኖረው ስለሚገባው ግንኙነት የሕግ ማዕቀፍ ለማውጣት ወሰነ፡፡

ምክር ቤቱ መስከረም 24 ቀን 2008 ዓ.ም. በመጀመርያ ጉባዔው አቶ ያለው አባተን በአፈ ጉባዔነት የመረጠ ሲሆን፣ አቶ መሐመድ ረሻድን በምክትል አፈ ጉባዔነት እንዲቀጥሉ መርጧቸዋል፡፡ በማግሥቱ መስከረም 25 ቀን ባካሄደው ጉባዔው የምክር ቤቱን የተለያዩ ቋሚ ኮሚቴዎች የ2008 ዕቅድ አዳምጧል፡፡

ከቋሚ ኮሚቴዎቹ መካከል የዴሞክራሲ አንድነት፣ የሕገ መንግሥት አስተምህሮና የሰላም ግንባታ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የዕቅድ ሪፖርቱን አቅርቧል፡፡

በአገሪቱ የፌዴራል ሥርዓት ውስጥ የፌዴራልና የክልል መንግሥታት በሕገ መንግሥቱ የተረጋገጡ ሥልጣንና ኃላፊነቶች ያሏቸው ቢሆንም፣ በሕገ መንግሥቱ መሠረት ደግሞ አንድ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ማኅበረሰብ መፍጠር እንደሚገባ ሕገ መንግሥቱ እንደሚደነግግ ቋሚ ኮሚቴው ገልጿል፡፡

አንድ የኢኮኖሚና የፖለቲካ ማኅበረሰብ በኢትዮጵያ ለመፍጠር ክልሎችና የፌደራል መንግሥታት የሚደጋገፉበትና የሚቀራረቡበት ሁኔታን መፍጠር እጅግ አስፈላጊ መሆኑን አስምሮበታል፡፡

ይኼ ግንኙነት ግን በተደራጀ መልኩ መመራት ያለበት በመሆኑ፣ ግንኙነቱ የሚመራበት የፖሊሲና የሕግ ማዕቀፍ የግድ ስለሆነ ማዕቀፉ በ2008 ዓ.ም. በማዘጋጀት ሕጉ እንዲወጣ እንደሚያደርግ ገልጿል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአማራ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ

እሑድ ጠዋት መስከረም 13 ቀን 2016 ዓ.ም. የፋኖ ታጣቂዎች...

ብሔራዊ ባንክ ለተመረጡ አልሚዎች የውጭ አካውንት እንዲከፍቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈቀደበት መመርያና ዝርዝሮቹ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የውጭ ምንዛሪ አጠቃቀምንና ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮችን...

እነ ሰበብ ደርዳሪዎች!

ከሜክሲኮ ወደ ዓለም ባንክ ልንጓዝ ነው። ሾፌርና ወያላ ጎማ...