Monday, March 27, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
- Advertisement -

ፌርማታ ፅሁፎች

ደራሲ ማን ነው?

ትኩስ ፅሁፎች

አንተ ባለቅኔ! አንተ ልብ-ወለድ ወላጅ

ሥነጽሑፍን ከሕዝብ ገንጥሎ ተራማጅ፡፡

       ከመካከል ቁመህ ደረትህን አትንፋ

       ወይ እሳቱን አንድድ ወይ እሳቱን አጥፋ…

ወይ ነፋሱን አግድ ወይ ነፋሱን ግፋ

ወይ ደመናን ጥረግ ወይ ደመናን አስፋ

ወይ ትንፋሽህን ዋጥ ወይም ትንፋሽ ትፋ፡፡

      ወይ ዐይንህን ግለጥ ወይ ዐይንህን ዝጋ

      ወይ ጀሮህን ድፈን ወይ ጀሮህን አትጋ፡፡

ወይ ታጠቅ ተፈሪ ወይም ታጠቅ ቁምጣ

ወይም ፀሐይ አግባ ወይም ፀሐይ አውጣ፡፡

      አልሚ-አጥፊ ተብለህ አብጅ ዘመድ ጓድ

      ሁለት የወደደ አያገኝም አንድ፡፡

  ነፋስ አንከባሎም ወደ አንዱ አይጎልትህ

   መጥፎና መልካሙን ሳይመርጥ ጭንቅላትህ፡፡

ሥነጽሑፍ የሕዝብ ናት የሰፊው ሕዝብ ምርጫ

የላትም ጉራንጉር የግል መሸጎጫ

የልፍኝ ቤት መግቢያ… የጓሮ በር መውጫ፡፡

     እና! የምንለው የደራሲው ብዕሩ

     ወይም ከሕዝብ ሆኖ ቀይ ይሁን መስመሩ፡፡

ከሕዝቡ ደም ነክሮ ይጻፍ የሕዝብ ዋይታ

ወይም ከውሃው ጠቅሶ በውሃው ግጥም ይምታ፡፡

    ከሁለቱ መርጦ ባንደኛው ካልጣፈ

    ለደሙም ለውሃውም ጠላት ነው የጦፈ፡፡

ግን ከመኸል ቁሞ መንገዱን ከዘጋ

ኸንጥ ይግባ ተገፍቶ ምን አለው ከእኛ

  • አያልነህ ሙላቱ ‹‹ወይ አንቺ አገር›› (2004)
- Advertisement -
- Advertisement -

ተጨማሪ ለማንበብ

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች