Sunday, March 26, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ኪንና ባህልየአንጋፋው ጋዜጠኛ ተክሉ ታቦር መጽሐፍ ዓርብ ይመረቃል

የአንጋፋው ጋዜጠኛ ተክሉ ታቦር መጽሐፍ ዓርብ ይመረቃል

ቀን:

የቀድሞው ሬዲዮ ኢትዮጵያና የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ጋዜጠኛ፣ በኋላም የማስታወቂያ ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ የነበሩት አቶ ተክሉ ታቦር ሕይወት ተራኪ መጽሐፋቸውን አሳተሙ፡፡

‹‹ተክሉ ታቦር በተክሉ ታቦር›› በሚል ርዕስ የቀረበው መጽሐፍ የጋዜጠኞችን ኅብረተሰብ ወቅታዊ ሕይወት ፈንጣቂ የሆነ፣ የራስን ሕይወት ተራኪ መጽሐፍ መሆኑ በማስታወቂያው ተገልጿል፡፡ መጽሐፉ ዓርብ መጋቢት 14 ቀን 2010 ዓ.ም. በ8፡30 ሰዓት በዋቢ ሸበሌ ሆቴል እንደሚመረቅም ታውቋል፡፡

አቶ ተክሉ በቀድሞው ሬዲዮ ኢትዮጵያ ለ10 ዓመት፣ ከ1967 ዓ.ም. በኋላ ለዘጠኝ ዓመት በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ሠርተዋል፡፡ በተለይም ‹‹የውይይት መድረክ›› በተሰኘው ፕሮግራማቸው ይታወቃሉ፡፡ ከሁለቱ የሚዲያ ተቋማት በኋላ በማስታወቂያ ሚኒስቴር የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ኃላፊ ሆነው ሠርተዋል፡፡

*****

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአልማዝ ኢዮቤልዩዐውደ ርዕይ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተመሠረተበትን 75ኛ ዓመት የአልማዝ ኢዮቤልዩ በዓል ምክንያት በማድረግ ያዘጋጀው የታሪካዊ ጉዞ ዐውደ ርዕይ ሐሙስ መጋቢት 13 ቀን 2010 .ም. በአዲስ አበባ ሙዚየም ይከፈታል፡፡ ዐውደ ርዕዩ ለተከታታይ 15 ቀናት ለተመልካቾች ክፍት ሆኖ እንደሚቆይ ባንኩ አስታውቋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ለፋይናንስ ዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የማፍራት የቤት ሥራን የማቃለል ጅማሮ

የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እያደገ ለመሆኑ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ  የግል...

የምድር ባቡርን የሚያነቃቃው የመንግሥት ውሳኔ

በኢትዮጵያ ወደብ አልባነት ላይ የተደመረውን የሎጀስቲክስ ችግር ለመፍታት ግዙፍ...

የፓርላማ አባላት ስለሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ግልጽ መረጃ የለንም አሉ

‹‹ሕወሓትን ለፍረጃ አብቅተውት የነበሩ ጉዳዮች በአብዛኛው መልክ ይዘዋል›› ሬድዋን...