Monday, September 25, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትለሪዮ ኦሊምፒክ መንግሥት ከጎኑ እንዲቆም ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ጠየቀ

ለሪዮ ኦሊምፒክ መንግሥት ከጎኑ እንዲቆም ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ጠየቀ

ቀን:

–    የሪዮ ኦሊምፒክ 296 ቀናት ይቀሩታል

ከዛሬ ጥቅምት 1 ቀን 2008 ዓ.ም. ተነሥተን ስንቆጥር በብራዚል ዘንድሮ የሚካሄደው የሪዮ 2016 ኦሊምፒክ ጨዋታዎች ሊጀመር 296 ቀናት ይቀሩታል፡፡ የዓለም ሁሉ ዓይንና ጆሮ ወደ ብራዚላዊቷ መዲና ሪዮ ዲጂኔሮም ይሆናል፡፡
የዓለም ቁጥር አንድ ቡና አምራች በሆነችው ብራዚል በሚካሄደው 31ኛው ኦሊምፒያድ የቡና መሠረት የሆነችው ኢትዮጵያ እንዳለፉት ኦሊምፒያዶች ሁሉ ተወዳዳሪ ሆና ለመገኘት ቅድመ ዝግጅት መጀመሩ ይታወቃል፡፡
እንደ ማሳያ ባለፈው ዓመት ለብሔራዊ ቡድን አሠልጣኞች፣ ለቴክኒክ ኃላፊዎችና ባለሙዎች እንዲሁም ለሐኪሞች በስፖርት ሜዲስን ሥልጠና መሰጠቱ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ከአትሌቲክስ ሌላ በብስክሌት ሁለት ተወዳዳሪዎች ፍቅረኛሞቹ ፅጋቡ ገብረ ማርያምና ሐድነት አስመላሽ እንደሚካፈሉ ተረጋግጧል፡፡

አዲሱ የኢትዮጵያ መንግሥት ካቢኔ መመሥረትና ስፖርት ኮሚሽንን ከወጣቶች ጋር ቀላቅሎና የወጣቶችና ስፖርት ሚኒስቴር መሆኑን ተከትሎ አዲሱ ሚኒስትር አቶ ሬድዋን ሁሴን ባለፈው ሳምንት ከኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ አመራሮች ጋር በኦሊምፒክ ኮሚቴው ጽሕፈት ቤት ምክክር አድርገዋል፡፡
ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴው በድረ ገጹ እንዳመለከተው፣ ፕሬዚዳንቱ አቶ ብርሃነ ኪዳነ ማርያም፣ የወጣቶችና ስፖርት ሚኒስቴር ጥቂት ወራት ለቀሩት የሪዮ ኦሊምፒክ ጨዋታዎች ከኦሊምፒክ ኮሚቴ ጎን በመሆን አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርግ ጥያቄ አቅርበዋል፡፡

ስለኦሊምፒክ ኮሚቴው አደረጃጀትና የአሠራር ሥርዓት ገለጻ የተደረገላቸው ሚኒስትሩ አቶ ሬድዋን ከኮሚቴው ጋር ተቀራርበው እንደሚሠሩ፣ የሪዮ 2016 ኦሊምፒክ ጨዋታዎች ዝግጅትና ተሳትፎ አስመልክቶ ሚኒስቴሩ በተደራጀ አግባብ ድጋፉን እንደሚያደርግ ቃል ገብተዋል፡፡
 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የቤት ባለንብረቶች የሚከፍሉትን ዓመታዊ የንብረት ታክስ የሚተምን ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ

በአዋጁ መሥፈርት መሠረት የክልልና የከተማ አስተዳደሮች የንብረት ታክስ መጠን...

እንደ ንብረት ታክስ ያሉ ወጪን የሚያስከትሉ አዋጆች ከማኅበረሰብ ጋር ምክክርን ይሻሉ!

የመንግሥትን ገቢ በማሳደግ ረገድ አስተዋጽኦ እንዳላቸው የሚታመኑት የተጨማሪ እሴት...

ለዓለምም ለኢትዮጵያም ሰላም እንታገል

በበቀለ ሹሜ ያለፉት ሁለት የዓለም ጦርነቶች በአያሌው የኃያል ነን ባይ...